ሠላሳ አራተኛ ዓመት ቍጥር ፳፫
መ ን ግ ሥ ት
ነ ጋ ሪ ት ፡ ጋ ዜ ጣ ።
የጋዜጣው ፡ ዋጋ ፤ ባገር • ውስጥ ' ባመት '
በ፮ ' ወር ', 3 ብር ያንዱ '
12 ብር
ማ ው ጫ ፲፱፻፷፯ ዓ. ም.
አዋጅ ቍጥር ፳፯ ፲፱፻፷፯ ዓ.ም.
የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት የተቋቋመበ ትን አዋጅና የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግንና የሊቀ መንበሩን ሥልጣን ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ለማሻሻል የወጣ አዋጅ
በጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ሊቀ መንበር ጽሕፈት ቤት ተጠባባቂነት የወጣ
ገጽ ፹፯
አዋጅ ቍጥር ፳፯ ፲፱፻፷፯ ዓ. ም.
ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት የተቋቋመበትን አዋጅና የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግንና የሊቀ መንበሩን ሥል ጣን ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ለማሻሻል የወጣ አ ዋ ጅ
« ኢትዮጵያ ትቅደም »
ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት በተቋቋመበት አዋጅ መሠ ረት የኢትዮጵያ ንጉሥ የሆኑት መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ከብዙ ጊዜ ጀምሮ ያደረባቸው የጤና ጉድለት ሀገርን የመም ራትን ያህል ከባድ ኃላፊነት ለመሸከም የማያስችላቸው መሆ ኑን በመረዳትና ፤
ለወደፊቱም ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት የመንግሥት ዓይ ነት በሕዝቡ የሚወሰን ጉዳይ ስለሆነ ፤
የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግንና የሊቀ መንበሩን ሥልጣን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቍጥር ፪ ፲፱፻፷፯ ዓ. ም. በአንቀጽ ፮ መሠረት ከዚህ የሚከተለው ታውጅዋል ።
፩ ፤ አጭር ርእስ ፤
ይህ አዋጅ « የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት የተቋቋመ በትን አዋጅና የጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግንና የሊቀ መንበሩን ሥልጣን ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቍጥር ፳፯ ፲፱፻፷፯ ዓ. ም. » ተብሎ ሊጠቀስ ይቻላል "
፪ ⋅ ማ ሻ ሻ ያ
(፩) ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት የተቋቋመበት አዋጅ ቍጥር ፩፲፱፻፷፯ ዓ. ም. እንደሚከተለው ተሻሽሏል ። አንቀጽ ፫ ተሠርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀጽ ፫ ተተ ክቷል "
አዲስ አበባ መጋቢት ፰ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ. ም.
ቢያንስ በወር አንድ ጊዜ ይታተማል የፖስታ ሣጥን ቍጥር ፩ሺ፴፩ (1031)