×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
አዋጅ ቁጥር 238/93 የኢትዮጵያ ግብርና ቆጠራ ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

ነጋሪት ጋዜጣ የሚተዳደር በመሆኑና ይህንኑ የተመለከተ መሠረታዊ የ 1 የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሰባተኛ ዓመት ቁጥር ፳፮ አዲስ አበባ ግንቦት ፳፫ ቀን ፲፱፻፫ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፰ ፲፱፻፶፫ ዓም : የኢትዮጵያ ግብርና ቆጠራ ኮሚሽን ማቋቋሚያ ገጽ ፭ሺ፭፻፲፩ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፪ / ፲፱፻፲፫ የኢትዮጵያ ግብርና ቆጠራ ኮሚሽንን ለማቋቋም የወጣ አዋጅ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ በግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ መረጃ በማስፈለጉ ፤ ዝርዝር የሆኑ የግብርና መረጃዎች መኖር በአገር አቀፍና በክልሎች ፣ ከዚያም በታች ባሉ የአስተዳደር እርከኖች ለሚቀየሱ | regarding the agricultural sector is essential for policy and ፖሊሲዎችና የልማት ፕሮግራሞች አፈጻጸም ፣ ክትትልና ቁጥጥር | evaluation at national , regional and at lower administrative አስተማማኝ መሠረት በመሆኑ ፤ ይህንኑ የቆጠራ ሥራ በተቀላጠፈና በአስተማማኝ ሁኔታ | operations efficiently and effectively , it is found necessary to ለመምራት በአገር አቀፍ ፣ በክልሎችና ከዚያም በታች ባሉ የአስተ | establish acommission that have a life span of upto five years , ዳደር እርከኖች ደረጃ በበላይነት የሚመራና የሚያስተባብር እስከ | and responsible for the overall management and coordination አምስት ዓመት ዕድሜ ያለው ኮሚሽን ማቋቋም በማስፈለጉ ፤ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመን ግሥት አንቀጽ ፶፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ፩ . አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የኢትዮጵያ ግብርና ቆጠራ ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፰ / ፲፱፻፶፫ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣ.ቁ : ፰ሺ፩ ) ” ..ራ ኮሚሽን / ከዚህ በኋላ ገጽ ሺ፩ሺ፭፻፲፪ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር፳ኘግንቦት፳፫ ቀን ፲፱፻፶ዓም ፪ . ትርጓሜ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም ካልተሰጠው በስተቀር በዚህ አዋጅ ውስጥ ፤ ፩ . “ የግብርና ቆጠራ ” ማለት በአገር አቀፍ ደረጃ ወይም በተወሰነ ብሔራዊ ክልል በተለይም ስለእርሻ መሬት ይዞታና የሰብል ምርት መጠን ፣ ስለቤት እንስሳትና ንብ በግብርና ሥራ ስለተሰማራው የሰው ኃይል ፣ ስለግብርና መሣሪያዎች ይዞታና አጠቃቀም ፣ ስለ መስኖ ሥራ፡ ምርጥ ዘር ፣ ማዳበሪያ ፣ ፀረ ተባይና ሌሎች ተመሳሳይ * ረጃዎችን አጠቃቀም በተመለከተ ወካይነት ባለው ከፍተኛ የናሙና መጠን በመጠቀም መሠረታዊ መረጃ ዎችን የመሰብሰብ፡ የማጠናቀር የመገምገም ፣ የመተን ተንና ውጤቱንም ለተጠቃሚዎችየማሠራጨትተግባር ፪ . “ ባለሥልጣን ” ማለት የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥ ልጣን ነው ፤ ፫ ኮሚሽን ” ማለት የግብርና ናሙና ቆጠራውን ሥራ በበላይነት እንዲመራና እንዲያስተባብር በማዕከል ፣ በክልል ፣ በዞንና በወረዳ የሚቋቋመው ኮሚሽን ነው ፤ ፬ ክልል ” ማለት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፵፯ የተጠቀሰው ማንኛውም ክልል ሲሆን ለዚህ አዋጅ አፈጻጸም ሲባል የአዲስ አበባና የድሬዳዋ መስተዳድርንም ይጨምራል ፤ ፭ “ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ” ማለት ማናቸውም የሚኒ ስቴር የኮሚሽን፡ የባለሥልጣን ፣ የጽሕፈት ቤት ፣ ተቋም ወይም ማናቸውም ሌላ የፌዴራል ወይም የክልል መንግሥት መሥሪያ ቤት ነው ፮ “ ሰው ” ማለት ማንኛውም የተፈጥሮ ሰው ወይም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው ድርጅት ነው ። ፫ ስለመቋቋም ፩ የኢትዮጵያ ግብርና “ ኮሚሽን ” ተብሎ የሚጠራ / በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል ። ፪ ኮሚሽኑ ተጠሪነቱ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ይሆናል ። ፫ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የቆጠራውን ሥራ ለማስፈጸም ደንብ የማውጣት ሥልጣን ይኖረዋል ። ፬ • የኮሚሽኑ አቋም ፩ • ኮሚሽኑ ፤ ሀ ) ማዕከላዊ ኮሚሽን ፣ ለ ) የብሔራዊ ክልል ኮሚሽን ሐ ) የዞን ኮሚሽን ፤ መ ) የወረዳ ኮሚሽን ፤ እና ሠ ) እንደ አስፈላጊነቱ የቀበሌ ኮሚቴዎች ፡ ይኖሩታል ። ፪ ባለሥልጣኑ የኮሚሽኑ ጽህፈት ቤት ሆኖ ያገለግላል ። የማዕከላዊ ኮሚሽኑ አባላት ማዕከላዊ ኮሚሽኑ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ፤ ፩ ጠቅላይ ሚኒስትር ተወካይ ፪ የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ሚኒስትር አባልና ም / ሰብሳቢ ፫ . የግብርና ሚኒስትር ፬ . የማስታወቂያና ባሕል ሚኒስትር ፭ የገንዘብ ሚኒስትር የግብርና ምርምር ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ፯ . የኢንቨስትመንት ጽ / ቤት ኃላፊ ..... ማለፉ \ ገጽ ፭ሺ፭፻፲፫ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፳፮ ግንቦት ፳፫ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓም • ፯ የትምህርት ሚኒስትር የውሀ ሀብት ሚኒስትር ፱ . የተፈጥሮ ሀብትና የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ፲ . የእንስሳትና የእንስሳት ተዋጽኦ ገበያ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ የቡናና ሻይ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አሥኪያጅ . ” ፲፪ . በጠቅላይ ሚ / ር ጽ / ቤት የክልል ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊ ፲፫ . የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ .... አባልና ፀሐፊ ። ፮ . የማዕከላዊ ኮሚሽኑ ሥልጣንና ተግባር ማዕከላዊ ኮሚሽኑ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባር ይኖረዋል ፤ ፩ . የኢትዮጵያ ግብርና ቆጠራን በሚመለከት የፖሊሲ መመሪያ ማውጣትና አፈጻጸማቸውን መከታተል ፤ ቆጠራ የሚከናወንበትን ጊዜና የሚሰበሰበውን የመረጃ ዓይነት መወሰን ፤ ፫ . ስለግብርና ቆጠራ ተግባር ለሕዝብ ማሳወቅ ፤ እና ፬ . ከብሔራዊ ክልል ኮሚሽን በሚቀርቡ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ መስጠት ። ፯ . የብሔራዊ ክልል ኮሚሽን አባላት የብሔራዊ ክልል ኮሚሽኑ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ፤ ፩ የክልሉ መንግሥት ፕሬዚዳንት .. .. ፪ . የፕላንና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ ... አባልና ም / ሰብሳቢ የግብርና ቢሮ ኃላፊ 6 • የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ፭ . የማስታወቂያ ቢሮ ኃላፊ ፮ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ... ፰ የፖሊስ ኮሚሽነር ፱ የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ቢሮ ጽ ቤት ; በክልሉ በግብርና እንቅስቃሴ ላይ የተሠማሩ ሌሎች ድርጅቶች ኃላፊ ....... የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥልጣን ቅርንጫፍ ጽ / ቤት ኃላፊ አባልና ፀሐፊ ። በዞንና በወረዳ ደረጃ የሚገኙ ኮሚሽኖች አባላት በዞንና በወረዳ የሚቋቋሙት ኮሚሽኖች አባላት ከክልል ኮሚሽኑ በሚወጣው መመሪያ መሠረት ይወሰናል ። የዞንና የወረዳ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴዎች ሊቃነመና ብርት እንደአግባቡ በዞንና በወረዳ ደረጃ ለሚቋቋሙ ኮሚሽኖች ሰብሳቢዎች ይሆናሉ ። ፫ . በየደረጃው የሚገኝ የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥ ልጣን ኃላፊ ወይም ተጠሪ እንደአግባቡ በዞንና በወረዳ ለሚቋቋመው ኮሚሽን ፀሐፊ ይሆናል ። በብሔራዊ ክልል ፣ በዞንና በወረዳ ደረጃ የሚገኙ ኮሚሽኖች ሥልጣንና ተግባር ፩ . በብሔራዊ ክልል ፣ በዞንና በወረዳ የሚቋቋመው ኮሚሽን ተጠሪነቱ በደረጃ ቀጥሎ ለሚገኘው የበላይ ኮሚሽን ሆኖ በየደረጃው የሚከተለው ሥልጣንና ተግባር ይኖረዋል ፣ ገጽ ሺ፩ሺ፭፻፲፬ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር፲ግንቦት፳፫ቀን ፲፱፻፫ዓ • ም • ሀ ) ከደረጃውቀጥሎከሚገኘው የበላይኮሚሽን የሚተ ላለፉ መመሪያዎች በሥራ ላይ መዋላቸውን የማረ ለ ) ለግብርናቆጠራው አፈጸጸም በየአስተዳደር እርከኑ ውስጥ የሚገኘውን ሕዝብ እንደዚሁምመ / ቤቶችና ድርጅቶች የመቀስቀስና የማስተባበር ፣ ሐ ) በየአስተዳደር እርከኑ ውስጥ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በማገናዘብ ለቆጠራው አፈጻጸም ስልቶችን የመቀየስ ፣ የሚያጋጥሙ ችግሮችን መፍታትና ለቆጠራው ስኬታማነት ሁኔታዎችን ማመቻቸት ፣ መ ) ከደረጃ ቀጥሎ ከሚገኘው የበላይ ኮሚሽን የሚሰጡ ሌሎች ተግባሮችን የማከናወን ። ፪ • በቀበሌ ደረጃ የሚቋቋመው ኮሚቴ ሥልጣንና ተግባር ኮሚሽኑ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት ይወሰናል ። ፲ የስብሰባና የውሳኔ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ፩ በየደረጃው የሚቋቋመው ኮሚሽን በሰብሳቢው ጥያቄ ወይም ከግማሽ በላይ የሆኑ የኮሚሽን አባላት ሲጠይቁ ይሰበሰባል ። ፪ ከኮሚሽኑ አባላት አብዛኛዎቹ ሲገኙ ምልዐተ ጉባዔ ይሆናል ። ፫ • የኮሚሽኑ ውሳኔ በድምፅ ብልጫ ይሆናል ። ድምፁ እኩል ለእኩል ከተከፈለ ሰብሳቢው ያለበት ወገን ወሳኝ ድምፅ ይኖረዋል ። ፬ • ኮሚሽኑ የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት ደንብ ያወጣል ። ነ፩ . የባለሥልጣኑ ሥልጣንና ተግባር ባለሥልጣኑ በማቋቋሚያ ሕግ ከተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት በተጨማሪ የግብርና ቆጠራው አስፈጸሚ ድርጅት ነው ። ይህ አጠቃላይ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ ባለሥ ልጣኑ የግብርና ቆጠራውን ለማከናወን የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ለግብርና ቆጠራው ሥራ የሚያስፈልጉ መጠይቆች ፣ መመሪያ ዎችና የመስክ መገልገያ ዕቃዎች የማዘጋጀት ፣ የግብርና ቆጠራውን የሚመለከቱ መረጃዎች የመሰ ብሰብ ፣ ለዚህም አግባብ ያላቸው ሠነዶችና መዛግብት የመመርመርና ምርመራውንም ለማከናወን አግባብ ባለው ጊዜ ሕግ በሚፈቅደው መሠረት ወደ ማንኛውም ሰው ቅጥር ግቢ ወይንም ይዞታ የመግባት ፣ በግብርና ቆጠራ የተሰበሰበውን መረጃ ማደራጀት ፣ መተ ንተንና ሪፖርቱን አዘጋጅቶ ለማዕከላዊ ኮሚሽኑ የማቅ ረብና ሲፈቀድም የማሠራጨት ፣ በዚህ አዋጅ በአንቀጽ ፲፩ ( ፪ ) መሠረት ቆጠራው እንዲ ካሄድ በተወሰነበት ጊዜ ውስጥ አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው አግባብ ካለው አካል ጋር በመመካከር በማንኛውም የመንግሥት መ / ቤት ሠራተኞች ፣ ንብረትና አገልግሎት ትብብር በመጠየቅ የመጠቀም ፣ ፭ የግብርና ቆጠራውን ዓላማ ከግቡ ለማድረስ አግባብ ያላቸው ሌሎች አስፈላጊ ተግባሮችን የማከናወን ። ገጽ ሺ፩ሺ፭፻፲፭ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር፳፮ ግንቦት ፳፫ ቀን ፲፱፻፫ ዓ.ም ፲፪ : የመተባበር ግዴታ ፩ . ማንኛውም ሰው በዚህ አዋጅ መሠረት ለሚከናወነው የግብርና ቆጠራ ሥራ የመተባበር ግዴታ አለበት ። በዚህ አዋጅ መሠረት መረጃ እንዲሰጥ የተጠየቀ ማንኛውም ሰው የባለሥልጣኑን መታወቂያ ለሚያሳይ መረጃ ሰብሳቢ ወይም ተቆጣጣሪ ትክክለኛውን መረጃ የመስጠት ግዴታ አለበት ። ፫ . ማንኛውም የቅጥር ግቢ ፣ የእርሻ ማሳ ፣ የከብቶችና የእርሻ መሣሪያዎች ባለንብረት ወይም ባለይዞታ ወይም ጠባቂ ወይም ወኪል ከባለሥልጣኑ የተሰጠውን መታወቂያ ለሚያሳይ የግብርና ቆጠራ መረጃ ሰብሳቢ ወይም ተቆጣጣሪ ወደ ተባለው ንብረት ወይም ይዞታ እንዲገባ የመፍቀድ ግዴታ አለበት ። ፲፫ የመረጃዎች ምሥጢራዊነት በፍርድ ቤት ካልታዘዘ በስተቀር ከግለሰቦችና ከድርጅቶች | 13. Confidentiality of the Information የተሰበሰቡትን የግብርና ቆጠራ ዝርዝር መረጃዎች ባለሥ ልጣኑ በምሥጢር ይጠብቃል ። ፲፬ . ቅጣት ማንኛውም ሰው ፣ ፩ . የግብርና ቆጠራን መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆነ ወይም ይህንኑ በሚመለከት ሐሰተኛመረጃ የሰጠ ፤ ወይም ፪ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፪ር ) የተደነገገውን በመተላለፍ መረጃ ሰብሳቢው ወይም ተቆጣጣሪው ወደተባለው ንብረት ወይም ይዞታ እንዲገባ ያልፈቀደ ፣ እንደሆነ ጥፋተኛ ሆኖ ሲገኝከ፩፻፲ብር ( አንድ መቶ ሃምሳብር ) ወይም ከአንድ ወር በማይበልጥ እሥራት ይቀጣል ። ፲፭ ተፈጻሚነት ስለማይኖራቸው ሕጐች ይህን አዋጅ የሚቃረን ማንኛውም ሕግ ተፈጻሚነት አይኖ ፲፮ አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከግንቦት ፳፫ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓም ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ ግንቦት ፳፫ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓም : ዶ / ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?