የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ
አስራ ሦስተኛ ዓመት ቁጥር ፴
አዲስ አበባ - ግንባት ፲ ቀን ፲፱፻፺፱ | በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፩፻፴፭ / ፲፱፻፺፱ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሠፈረ ንብረት ስለሚከፈል ካሣ የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ገጽ ፫ሺ፮፻፳፪
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፩፻፭ / ፲፱፻፺፱ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሠፈረ ንብረት ስለሚከፈል ካሣ የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር ፬፻፸፩ / ፲፱፻፺፰ አንቀጽ ፭ እና ለህዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትንና ለንብረት ካሣ የሚከፈልበትን ሁኔታ ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር ፬፻፶፭ / ፲፱፻፺፯ አንቀጽ
፲፬ (፩) መሠረት ለህዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሰፈረ ንብረት የሚከፈል ካሳ ከንብረቱ የሚያስችል የመፈናቀያ ካሳ የሚያገኝበትን ሁኔታ
ለመደንገግ ይህንን ደንብ አውጥቷል ፡፡
ያንዱ ዋጋ
ክፍል አንድ
፩. አጭር ርዕስ
ይህ ደንብ “ ለህዝብ ጥቅም ሲባል በሚለቀቅ መሬት ላይ ለሰፈረ ንብረት ስለሚከፈል ካሣ የወጣ የሚኒ ስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፩፻፴፭ / ፱፻፺፱ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ፡፡
፪. ትርጓሜ
የቃሉ አግባብ ሌላ ትርጓሜ የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ ደንብ ውስጥ ፧
ነጋሪት ጋዜጣ ፖ.ሣ.ቁ. ፹ሺ፩