የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ አራተኛ ዓመት ቁጥር ፪ አዲስ አበባ ሰኔ ፳ ቀን ፲፱፻፲ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ ኣዋጅ ቁጥር ፩፻፳፬ / ፲፱፻፲ ዓም ለትምህርት ልማት ፕሮግራም ከፊል ማስፈጸሚያ ከዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር ብድር ለማግኘት የተፈረመው የብድር ስምምነት ማጽደቂያ አዋጅ . . . . . . . ገጽ ፯፻፵፮ አዋጅ ቁጥር ፩፻፳፬ / ፲፱፻፲ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረገውን የብድር ስምምነት ለማጽደቅ የወጣ አዋጅ ለትምህርት ልማት ፕሮግራም ከፊል ማስፈጸሚያ የሚውል መጠኑ ኤስዲ - ኣር ጀ፱ ሚሊዮን ፫፻ሺህ ( ሰባ አራት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሺህ ኤስዲ - ኣር ) የሆነ ገንዘብ የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለም አቀፍ የልማትማኅበር መካከልእ . ኤአ . ጁን ፬ ቀን ፲፱፻፲፰ ዋሽንግተን ዲሲ የተፈረመ በመሆኑ ፡ መሠረታዊ የኢኮኖሚ ዓለምአቀፍ ውሎች ተፈጻሚ ከመሆናቸው በፊት መጽደቅ ስላለባቸው ፡ ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ ፳፫ ቀን ፲፱፻፶ ዓም : ባደረገው ስብሰባው ያጸደቀው ስለሆነ ፡ በሕገመንግሥቱ አንቀጽ ፶፭ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እና ( ፲፪ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ ሸሺ፩ ገጽ Lየንጊ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፬ ሰኔ ፳፫ ቀን ፲፱፻፲ ዓም• አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ ለትምህርት ልማት ፕሮግራም ከፊል ማስፈጸሚያ ከዓለም አቀፍ የልማት ማኀበር ብድር ለማግኘት የተፈረመው የብድር ስምምነት ማጽደቂያ አዋጅ ቁጥር ፩፻፳፬ / ፲፱፻፲ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። በዚህ አዋጅ ውስጥ “ የብድር ስምምነት ” ማለት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል እ ኤ . ኣ . ጁን ፬ ቀን ፲፱፻፲፰ በዋሽንግተን ዲሲ የተፈረመው ቁጥር ፫ ሺህ ሮ ኢት• የብድር ስምምነት ነው ። የገንዘብ ሚኒስትር ሥልጣን የገንዘብ ሚኒስትሩ በብድር ስምምነቱ የተገኘውን ኤስዲአር ሮ፱ ሚሊዮን ፫፻ሺህ ( ሰባ አራት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሺህ 1 ኤስዲ - አር ) በብድር ስምምነቱ በተመለከቱት ሁኔታዎች መሠረት በሥራ ላይ እንዲውል ለማድረግ በዚህ አዋጅ ሥልጣን | 4 . Effective Date ተሰጥቶታል ። ፬ አዋጁ የሚጸናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከሰኔ ፳፫ ቀን ፲፱፻፲ ዓ ም ጀምሮ የጸና ይሆናል ። ኣዲስ ኣበባ ሰኔ ፳፫ ቀን ፲፱፻፲ ዓ . ም ዶ ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ