×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 26/1990 9.7 ዝቋላ ስቲል ሮሚን፡ሚል ትልቅ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ አራተኛ ዓመት ቁጥር ፲፪ አዲስ አበባ ጥር ፳፮ ቀን ፲፱፻፲ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ጠባቂነት የወጣ ደንብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፳፮ ፲፱፻፲ ዓ.ም ዝቋላ ስቲል ሮሊንግ ሚል ድርጅት ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ገጽ ፮፻፳፭ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፳፮ ፲፱፻፲ ዝቋላ ስቲል ሮሊንግ ሚል ድርጅትን ለማቋቋም የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራ ሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱ T ፯ አንቀጽ ፭ እና በመንግሥት የልማት ድርጅቶች አዋጅ ቁጥር ፳፭ ፲፱፻፲፬ አንቀጽ ፯ ፩ ሀ መሠረት ይህን ደንብ አውጥቷል ። ፩ . አጭር ርዕስ ይህ ደንብ “ ዝቋላ ስቲል ሮሊንግ ሚል ድርጅት ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፳፮ ፲፱፻፲ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ : መቋቋም ፩ ዝቋላ ስቲል ሮሊንግ ሚል ድርጅት ( ከዚህ በኋላ “ ድርጅቱ ” እየተባለ የሚጠራ ) የመንግሥት የልማት ድርጅት ሆኖ በዚህ ደንብ ተቋቁሟል ። ፪ • ድርጅቱ በመንግሥት የልማት ድርጅቶች አዋጅቁጥር፳፭ ፲፱፻፳፬ መሠረት ይተዳደራል ። ፫ . ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን በመንግሥት የሚሰየም አካል የድርጅቱ ተቆጣጣሪ ባለሥ ልጣን ይሆናል ። ያንዱ ዋጋ ብር 2:30 ነጋሪት ጋዜጣ ፖ.ሣ.ቁ : T ሺ፩ ገጽ ፮፻፷፮ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፪ ጥር ፳፮ ቀን ፲፱፻፲ ዓም ፬ . ዋና መሥሪያ ቤት የድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት በደብረዘይት ይሆናል ፤ እንዳስፈላጊ ነቱም በማናቸውም ሥፍራ ቅርንጫፍ ሊኖረው ይችላል ። ፭ ዓላማ የድርጅቱ ዓላማ የአርማታ ( ሪንፎርስመንት ) ብረቶችና ስትራክ ቸራል ስቲል ማምረትና ለገበያ ማቅረብ፡ በተጨማሪም ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚረዱ ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎችን መሥራት ነው ። ፮ ካፒታል ለድርጅቱ የተፈቀደለት ካፒታል ብር ፪፻፴፫ሚሊዮን፰፻፵፩ሺህ ፮፻፲፪ብርጀ፩ ( ሁለት መቶ ሠላሳ ሦስት ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ አንድ ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና ሁለት ብር ከሰባ አንድ ሣንቲም ) ሲሆን ከዚህ ውስጥ ብር ዥ፫ሚሊዮን፰፻፵፩ሺህ፮፻፯ ፪፻፩ ( ሰማንያ ሦስት ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ አንድ ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና ሁለት ብር ከሰባ አንድ ሣንቲም ) በጥሬ ገንዘብና በዓይነት ተከፍሏል ። ፯ ኃላፊነት ድርጅቱ ካለው ጠቅላላ ንብረት በላይ በዕዳ ተጠያቂ አይሆንም ። ፰ : ድርጅቱ የሚቆይበት ጊዜ ድርጅቱ ላልተወሰነ ጊዜ ይቆያል ። ፱ • ደንቡ የሚጸናበት ጊዜ ይህ ደንብ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ ጥር ፳፮ ቀን ፲፱፻፲ ዓ.ም መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?