የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ አምስተኛ ዓመት ቁጥር ፩ አዲስ አበባ መስከረም ፳፪ ቀን ፲፱፻፲፩ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፴፩ / ፲፱፻፲፩ ዓ.ም የቆዳና የቆዳ ውጤቶች ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ገጽ ፰፻፵፰ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፵፩ / ፲፱፻፲፩ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ለማቋቋም የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራ ሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፷፯ አንቀጽ ፭ መሠረት ይህን ደንብ አውጥቷል ። ፩ . አጭር ርዕስ ይህ ደንብ “ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፴፩ ፲፱፻፲፩ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ . ትርጓሜ በዚህ ደንብ ውስጥ “ ሚኒስቴር ” ወይም “ ሚኒስትር ” ማለት እንደ ቅደም ተከተሉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ወይም ሚኒስትር ነው ። ፫ መቋቋም የቆዳና የቆዳ ውጤቶች ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከዚህ በኋላ “ ኢንስቲትዩቱ ” ተብሎ የሚጠራ / የሕግ ሰውነት ያለው ራሱን የቻለ የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤት ሆኖ በዚህ ደንብ ተቋቁሟል ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ ዥሺ፩ ኢሎች ተግባ ገጽ ፰፻፬ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፩ መስከረም ፳፪ ቀን ፲፱፻፷፩ ዓም • ፪ • የኢንስቲትዩቱ ተጠሪነት ለሚኒስቴሩ ይሆናል ። ፬ • የኢንስቲትዩቱ ዋና መሥሪያ ቤት የኢንስቲትዩቱ ዋና መሥሪያ ቤት በአዲስ አበባ ከተማ ይሆናል ፡ እንደአስፈላጊነቱም በሌሎች ቦታዎች ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶች ማቋቋም ይችላል ። ፭ የኢንስቲትዩቱ ዓላማ የኢንስቲትዩቱ ዓላማ ስለተለያዩ የቆዳና የቆዳ ውጤቶች አሠራር፡ከቆዳና ከቆዳ ውጤቶች ፋብሪካ ጋር ስለተገናኙጥሬ ዕቃዎች : ኬሚካልና መካኒካል አሠራሮች እና ስለጥራት ቁጥጥር ዘዴዎች የተግባርና የፅንሰ - ሀሣብ ሥልጠናዎችን በመስጠት እንዲሁም በመስኩ የምርምርና የምክር አገል ግሎት ሥራዎች በማካሄድ ለዘርፉ የሠለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ይሆናል ። ፮ . የኢንስቲትዩቱ ሥልጣንና ተግባር ለሌሎች የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በሕግ ተለይተው የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች እንደተጠበቁ ሆነው ኢንስቲ ትዩቱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ ፩ . በተለያዩ ደረጃዎች የቆዳና የቆዳ ውጤቶች ቴክኖሎጂ ሥልጠናዎችን በመስጠት በዘርፉ የሙያተኞችን ብዛት ማሳደግ ፡ ፪ • የቆዳና የቆዳ ውጤቶችን ጥራትና ብዛት ለማሳደግ የሚያስችሉ የምርምርና ልማት ተግባራትን ማከናወን ፤ ፫ የቆዳና የቆዳ ውጤቶችን የጥራት ደረጃ ለማሳደግ የሚያ ስችሉ የምክር አገልግሎቶችን መስጠት ፡ ፬ የዘርፉን ልማት ለማሳደግ የሚያስችሉ የመረጃ አገልግሎ ቶችን መስጠት ፡ ፭፡ ለሚያሰለጥናቸው ባለሙያዎች የምስክር ወረቀት መስጠት ፡ ፮ : ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች ክፍያ ማስከፈል ፤ ፯ የንብረት ባለቤት መሆን ፡ ውል መዋዋል ፣ በራሱ ስም መክሰስ እና መከሰስ ፡ ፰ ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚያስፈልጉ ራትን ማከናወን ። ፯ . የኢንስቲትዩቱ አቋም ኢንስቲትዩቱ፡ የሥራ አመራር ቦርድ ( ከዚህ በኋላ “ ቦርዱ ” እየተባለ የሚጠራ ) ፡ ፪ • በሚኒስትሩ አቅራቢነት በመንግሥት የሚሾም አንድ ዲሬክተር ፡ ፫ አካዳሚክ ካውንስል ፡ እና ፬ አስፈላጊ ሠራተኞች ፡ ይኖሩታል ። ፰ : የቦርዱ አባላት ቦርዱ ከመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና ከግሉ ዘርፍ የተውጣጡ በመንግሥት የሚሰየሙ ሰባት ኣባላት ይኖሩታል ፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ከአባላቱ መካከል በመንግሥት ይመደባል ። ገጽ ፰፻፶ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፩ መስከረም ፳፪ ቀን ፲፱፻፵፩ ዓም ፱ • የቦርዱ ሥልጣንና ተግባር ቦርዱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ ፩ . የኢንስቲትዩቱን ሥራዎች በበላይነት የመቆጣጠር ፣ የመከታተል እና ኢንስቲትዩቱ በዓላማው መሠረት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረጉን የማረጋገጥ ፤ ፪ • የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግን መሠረታዊ መርሆዎች በመከተል የኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች የሚቀጠሩበትንና የሚተዳደሩበትን መመሪያዎች የማፅደቅ ፡ የሠራተ ኞችን የደመወዝ ስኬልና ሌሎች የማነቃቂያ ክፍያዎችን የመወሰን ፣ ተግባራዊነታቸውንም የመከታተል ! ፫ ለዲሬክተሩ በቀጥታ ተጠሪ የሆኑ ኃላፊዎችን ቅጥር ፣ ምደባና ስንብት የማፅደቅ ፣ ፬ • ኢንስቲትዩቱ ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች የሚያስከፍ ለውን የክፍያ ተመኖች የመወሰን ፤ ፭ ኢንስቲትዩቱ ከአገር ውስጥ ወይም ከውጭ አገር ተቋማት ጋር የሚያደርጋቸውን ስምምነቶች የማፅደቅ ፤ ፮ የኢንስቲትዩቱን የሥራ ፕሮግራምና በጀት ለሚኒስቴሩ የማቅረብ ፣ ሲፈቀድም ተግባራዊነቱን የመቆጣጠር ፤ ፯ ይህንን ደንብ መሠረት በማድረግ የሚዘጋጁ የኢንስቲት ዩቱን የውስጥ ደንቦች የማፅደቅ ፣ ተግባራዊነታቸውንም የመከታተል ፤ ፰ በኢንስቲትዩቱ ዲሬክተር በሚቀርቡ ሌሎች የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ የመምከር ፣ የመወሰን ፣ ፬ ለኢንስቲትዩቱ ዲሬክተር አጠቃላይ የሥራ መመሪያ የመስጠት ፣ ፲ የኢንስቲትዩቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በየሩብ ፲ የቦርዱ ስብሰባ ፩ : ቦርዱ በወር አንድ ጊዜ ስብሰባ ይኖረዋል ፤ ሆኖም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በማናቸውም ጊዜ አስቸኳይ ስብሰባ ሊጠራ ይችላል ። በቦርዱ ስብሰባ ላይ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት አባላት ከተገኙ ምልዐተ ጉባዔ ይሆናል ። ፫ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ቦርዱ ውሳኔ የሚሰጠው በድምፅ ብልጫ ይሆናል ፤ ሆኖም ድምፅ እኩል ለእኩል የተከፈለ ከሆነ ሰብሳቢው ወሳኝ ድምፅ ይኖረዋል ። የዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ቦርዱ የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት ደንብ ሊያወጣ ይችላል ። የዲሬክተሩ ሥልጣንና ተግባር ፩ ዲሬክተሩ የኢንስቲትዩቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆኖ ከቦርዱ በሚሰጠው አጠቃላይ መመሪያ መሠረት የኢን ስቲትዩቱን ሥራዎች ይመራል ፣ ያስተዳድራል ። ፪ . በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) የተመለከተው አጠቃላይ አነጋገር እንደተጠበቀ ሆኖ ፡ ዲሬክተሩ፡ ሀ ) በዚህ ደንብ አንቀጽ ፮ የተመለከቱትን የኢንስቲት ዩቱን ሥልጣንና ተግባሮች ሥራ ላይ ያውላል ፤ ለ ) የኢንስቲትዩቱን የሠራተኞች አስተዳደር መመሪያ ፣ የደመወዝ ስኬልና ሌሎች የማነቃቂያ ክፍያዎች አጥንቶ ለቦርዱ ያቀርባል ፣ ሲፈቀድም ተግባራዊ ያደርጋል ፡ ገጽ ፰፻፶፩ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፩ መስከረም ፳፪ ቀን ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. ሐ ) የኢንስቲትዩቱን የሥራ ፕሮግራምና በጀት አዘጋጅቶ ለቦርዱ ያቀርባል : ሲፈቀድም ተግባራዊ ያደርጋል ፡ መ ) ለኢንስቲትዩቱ በተፈቀደው በጀትና የሥራ ፕሮግራም መሠረት ገንዘብ ወጪ ያደርጋል ፤ ሠ ) ከሦስተኛ ወገኖች ጋር በሚደረጉ ግንኙነቶች ኢንስቲትዩቱን ይወክላል ፤ ረ ) የኢንስቲትዩቱን የሥራ አፈፃፀምና የሂሣብ ሪፖርት አዘጋጅቶ ለቦርዱ ያቀርባል ። ፫ ዲሬክተሩ ለኢንስቲትዩቱ ሥራ ቅልጥፍና በሚያስ ፈልግ መጠን ሥልጣንና ተግባሩን በከፊል ለኢንስቲ ትዩቱ ሌሎች ኃላፊዎችና ሠራተኞች በውክልና ሊሰጥ ይችላል ። ፲፪ . ስለአካዳሚክ ካውንስል አባላት የኢንስቲትዩቱ አካዳሚክ ካውንስል የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል፡ ፩ . የኢንስቲትዩቱ ዳሬክተር ፪ . ሬጅስትራር . ፫ የተማሪዎች ተወካይ የመምህራን ተወካይ ፭ . ከኢንስቲትዩቱ ልዩ ልዩ ክፍሎች በቦርዱ የሚሰየሙ ተወካዮች ፲፫፡ የአካዳሚክ ካውንስሉ ሥልጣንና ተግባር የአካዳሚክ ካውንስሉ የሚከተሉት ሥልጣንና ተገባሮች ይኖሩታል፡ ፩ . የኢንስቲትዩቱን ልዩ ልዩ የትምህርት ፕሮግራምና ካሌንደር መርምሮ ለቦርዱ የማቅረብ ፡ ፪ • ዲፕሎማ ፡ ሠርቲፊኬትና ልዩ ሽልማት የሚሰጥበትን ሁኔታ እያጠና ለቦርዱ የማቅረብ ፡ ፫ . የተማሪዎችና ሠልጣኞች አቀባበልን ፡ የትምህርት ደረጃ አወሳሰንን : ምዘናን፡ የዲሲፕሊንና የምረቃ ጉዳዮችን የሚመለከቱ መመዘኛ መስፈርቶችን አዘጋጅቶ ለቦርዱ የማቅረብ ፡ ሲፈቀድም ተግባራዊ የማድረግ ፡ በነዚህ ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ አቤቱታዎ ችንና ቅሬታዎችን መርምሮ ውሳኔ የመስጠት ፡ ፬ አጠቃላይ የፈተና አሰጣጥ ዘዴና ሁኔታን የመወሰን ፡ ፭ . ስለአካዳሚክ እድገቶች ጉዳይ አጥንቶ የማቅረብ፡ ወደሚቀጥለው የትምህርት እርከን የሚሸጋገሩ ተማሪ ዎችን ዝርዝር መርምሮ የመወሰን ፡ የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት ደንብ የመወሰን ፡ በቦርዱ የሚሰጡትን ሌሎች ተግባሮች የማከናወን ። ፲ 0 በጀት የኢንስቲትዩቱ በጀት ከሚከተሉት ምንጮች የተውጣጣ ይሆናል ፡ ፩ በፌዴራል መንግሥት ከሚመደብለት የገንዘብ ድጎማ ፡ ፪ ከሚሰበሰበው የአገልግሎት ክፍያ፡ እና ፫ • ከዕርዳታ፡ ከስጦታ እና ከማናቸውም ሌሎች ምንጮች ከሚያገኘው ገቢ ። የሂሣብ መዛግብት ፩ . ኢንስቲትዩቱ የተሟሉና ትክክለኛ የሆኑ የሂሣብ መዛግብት ይይዛል ። ገጽ ፰፻፶፪ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፩ መስከረም ፳፪ ቀን ፲፱፻፵፩ ዓ • ም • ፪ የኢንስቲትዩቱ የሂሣብ መዛግብትና ገንዘብ ነክ ሰነዶች በዋናው ኦዲተር ወይም እርሱ በሚሰይመው ኦዲተር በየዓመቱ ይመረመራሉ ። ደንቡ የሚፀናበት ጊዜ ይህ ደንብ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ መስከረም ፳፪ ቀን ፲፱፻፶፩ ዓም • መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር