×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
የኢትዮጵያ ማህበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ ማቋቋሚያ አዋጅ ፲፱/፲፱፻፹፰

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ሁለተኛ ዓመት ቁጥር ፯ አዲስ አበባ የካቲት ፭ ቀን ፲፱፻፳፰ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፲፱ ፲፱የጤ፰ ዓም | የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ ማቋቋሚያ አዋጅ አዋጅ ቁጥር ፲፬ ፲፱፻፳፰ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ ለማቋቋም የወጣ አዋጅ የገጠሩ ድሀ ሕብረተሰብ መሠረታዊ የሆኑ ማኅበራዊ አገልግ ሎቶች የማግኘት በሩ እንዲከፈትለትና ኢኮኖሚያዊ መሠረተ ልማቶችና አገልግሎቶች ተዘርግተውለት ገቢውን ማሳደግ እንዲችል መርዳት አስፈላጊ በመሆኑ ፤ _ ይህ ዓላማ ግብ እንዲመታ በሙከራ መልክ ተቋቁሞ የነበ | infrastructure and services ; ረውን የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶ ፈንድ ወደ አገር አቀፍ ፕሮግራም ደረጃ ማስፋፋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፤ ይህን ፕሮግራም በሥራ ላይ ለማዋልና ፕሮጀክቶችን በማመ ንት ፣ በመቅረጽና ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ከታች ወደ ላይ የአሰራር ሥልትን በመከተል ለመስራት የሚችል የማኔጅመንት አካል መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፤ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፶፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ክፍል አንድ ፩ . አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ፲፱ ፲፱፻T፰ ” ተብሎ ሊጠቀስ | 1 . Short Title ይችላል ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣ . ቁ : ዥሺ፩ ገጽ ፻፯ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፯ የካቲት ፭ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ . ም ፪• ስለ መቋቋም ፩ . የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ ( ከዚህ በኋላ | 1 ) There is hereby established the Ethiopian Social “ ፈንዱ ” እየተባለ የሚጠራ ) የሕግ ሰውነት ያለው ፥ ራሱን የቻለ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሆኖ በዚህ አዋጅ ፪ የፈንዱ ተጠሪነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሆናል ። ፫• የፈንዱ ዓላማዎች የፈንዱ ዓላማዎች የሚከተሉት ይሆናሉ ፡ ፩ መሠረታዊ የሆኑ ማኅበራዊ አገልግሎቶችን በማቅረብና | በማጠናከር በዋነኛነት የገጠሩን ሕዝብ የኑሮ ደረጃ ማሻሻል ፣ ፪• የኢኮኖሚ መሠረተ ልማቶችንና አገልግሎቶችን በመዘር ጋትና በማቅረብ የድሃውን ሕብረተሰብ ገቢ የማግኘት አቅም ማሳደግ ፣ ፫ . ማኅበረሰብን መሠረት ያደረጉ ፕሮጀክቶችን የመለየት ፡ የማዘጋጀትና የመተግበር ፡ የማስተዳደርና የመንከባከብ ዘይቤን በሕብረተሰቡ ውስጥ ማራመድ ፡ ፬• ቀጣይነት ያለው አነስተኛ ብድር ለድሃው ሕብረተሰብ መስጠት የሚችሉ አነስተኛ ብድር ሰጪ ድርጅቶች እንዲፈጠሩና እንዲዳብሩ መርዳት ፡ ፭ ሕብረተሰቡን አግዘው የሚሰሩ መሠረታዊ ድርጅቶችንና ማኅበረሰቦችን በፕሮጀክት ሥራዎች ቴክኒካዊና የሥራ አመራር ብቃት እንዲያዳብሩ መርዳት ። ፬• የፈንዱ ሥልጣንና ተግባር ፈንዱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፡ ፩ መሠረታዊ የሆኑ ማኅበራዊ አገልግሎቶችን ለማቋቋምና | ለማጠናከር እርዳታ መስጠት ፡ ፪• በአካባቢ ደረጃ በሚከናወኑ ንዑስ ፕሮጀክቶች አማካይነት የሥራ ዕድል መፍጠርና በሙከራ ደረጃ በሚከናወነው የአነስተኛ ብድር አገልግሎት አማካይነት ድሃው የገጠር ሕዝብ ቀጣይነት ባለው የገቢ ማግኛ ሥራ ላይ እንዲሰማራ መርዳት ፡ ፫ የሥልጠናፕሮግራሞችለሕብረተሰቡ በማዘጋጀት መሠረታዊ የሕብረተሰብ ድርጅቶችንና ሕብረተሰቡን በማንኛውም የፕሮጀክት ሥራ ላይ ለመሳተፍ ያለውን አቅምማጎልበት ፣ ፬ . ሴቶች በማንኛውም የፕሮጀክት ሥራ እንቅስቃሴ እንዲ ሳተፉማበረታታት ፡ ፭ የንብረት ባለቤት መሆን ፡ ፮ . ውል መዋዋል ፡ – በስሙ መክሰስና መከሰስ ፡ ፰ ዓላማውን ከግቡ ለማድረስ የሚያስፈልጉ ሌሎች ተግባ ሮችን ማከናወን ። ፭ የፈንዱ አደረጃጀት ፩ . በማዕከላዊ ደረጃ ፡ ሀ ) የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ ቦርድ ( ከዚህ በኋላ “ ቦርዱ ” እየተባለ የሚጠራ ) ፡ ለ ) ማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት ፡ ሐ ) የፈንዱዋናሥራአስኪያጅ ፡ ምክትል ዋና ሥራአስኪያጅ እና አስፈላጊው የሰው ኃይል ይኖሩታል ። ገጽ ፻፰ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፯ የካቲት ፭ ቀን ፲፱፻ዥ፰ ዓም ፪ በእያንዳንዱ ክልል ! ሀ ) የክልል አስተባባሪ ኮሚቴ ' ለ ) የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት ' ሐ ) የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ' እንደ አስፈላጊነቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ እና አስፈ ላጊው የሰው ኃይል ይኖሩታል ። ክፍል ሁለት የፈንዱ ማዕከላዊ አካላት ፮• የቦርዱ አባላት ቦርዱ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ፣ ፩ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይም ተወካዩ . . . . . . . . ፪• በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የክልል ጉዳይ ዘርፍ ኃላፊ . . . . . . . . . . . . . . . . ፫ የገንዘብ ሚኒስትር . . . . . . . . . ፬• የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ሚኒስትር . . . ፭ . የውሀ ሀብት ሚኒስትር ፮ የግብርና ሚኒስትር . . . ፯ የፈንዱ ዋና ሥራ አስኪያጅ . . . . . . . . . . . . . . . . አባልና ፀሐፊ ፯ የቦርዱ ሥልጣንና ተግባር ፩ ቦርዱ የፈንዱን አጠቃላይ አስተዳደርና የሥራ ክንውን | 7 . ይመራል ፡ ይቆጣጠራል ። ፪ ከላይ የተጠቀሰው አጠቃላይ ሁኔታ ሳይወሰን ፡ ቦርዱ ፣ ሀ ) ፖሊሲዎች ፣ የአፈጻጸም መመሪያና በመመሪያው ላይ | የሚደረጉ ማሻሻያዎችን ጭምር ያወጣል ፡ ለ ) ዓመታዊ በጀትና የሥራ ፕሮግራም ያጸድቃል ፡ ሐ ) ዓመታዊ የሂሣብ ሪፖርት ያጸድቃል ፡ መ ) የሠራተኞችን የደመወዝ ስኬል ይወስናል ፡ ሠ ) የፈንዱ አጠቃላይ እንቅስቃሴ በተቀላጠፈና በሰከነ ሁኔታ ሊፈጸም ይችል ዘንድ የክልል መስተዳድሮ ችንና የልዩ ልዩ የፌዴራሉ መንግሥት ተቋማትን ትብብር ያስገኛል ፡ ረ ) ፈንዱን በሚመለከቱ ሌሎች የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ይሰጣል ። ፰ የቦርዱ ስብሰባ ፩ ቦርዱ በሦስት ወር አንድ ጊዜ ይሰበሰባል ። ሆኖም | 8 . Meetings of the Board በሰብሳቢው ጥሪ የቦርዱ አስቸኳይ ስብሰባዎች በማን ኛውም ጊዜ ሊደረጉ ይችላሉ ። ፪ ከቦርዱ አባላት ከግማሽ በላይ በስብሰባው ላይ ሲገኙ ምልዐተ ጉባኤ ይኖራል ። ፫• የቦርዱ ውሳኔ በስብሰባው ላይ በተገኙ አባላት በድምፅ ብልጫ ይሰጣል ። ድምዕ እኩል ለእኩል ከተከፈለ ሰብሳቢው ያለበት ወገን ወሳኝ ድምዕ ይኖረዋል ። [ ፬ ቦርዱ የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት ደንብ ሊያወጣ ይችላል ። ፬ . የማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት ሥልጣንና ተግባር የፈንዱ ማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፡ ፩ የፈንዱ እንቅስቃሴዎች በመላው አገሪቱ እንዲታወቁ ማድረግ ፡ ፪• በፕሮጀክቶች ዝግጅት : ማስተዋወቅ ፡ ግምገማ ፡ | አፈጻጸም ፡ ቁጥጥርና ክትትል ረገድ ብቃታቸውን ከፍ እንዲያደርጉ የክልል ጽሕፈት ቤቶችን መርዳት ፣ ፫ የፈንዱን ዓመታዊ በጀትና የሥራ ፕሮግራም አዘጋጅቶ | በማጠናቀር ለቦርዱ ማቅረብ ፡ ገጽ የ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፯ የካቲት ፭ ቀን ፲፱የተ፰ ዓ . ም . Federal Negarit Gazeta No . 7 - 13 February 1996 – Page 109 0 የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤቶችን የበጀትና የሥራ ፕሮግራም አፈጻጸም እንዲሁም የፋይናንስ እንቅስቃሴ መከታተልና በፈንዱ የሥራ መመሪያ መሠረት መከናወናቸውን ማረጋገጥ ፣ ፭ ለማዕከላዊው ጽሕፈት ቤት በጸደቀው በጀት መሠረት ክፍያዎችን መፈጸም : ፮ . ከክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤቶች የሚቀርቡ የመተኪያ ክፍያ ጥያቄዎችን ገምግሞ ለፋይናንስ አቅራቢ ምንጮች ማስተ ላለፍ ፡ ጊ ከውጭ አገር የሚያስፈልጉ ግዥዎችን ማከናወንና ክፍያ _ ዎችን መፈጸም ፣ ፲ - የፈንዱን የሥራ ፡ የፋይናንስ እንቅስቃሴና ወጪዎችን በተመለከተ የሩብ ዓመት ፡ የግማሽ ዓመትና ዓመታዊ ሀ - አጠቃላይ የፈንዱን አቅም ግንባታ ፡ ሥልጠናና ምርምር መርሐ ግብሮችን ማስተዳደር ፡ 1 . ፈንዱን የሚመለከቱ የፖሊሲ ሃሳቦችን ለቦርዱ ማቅረብ ፡ 16 - የፈንዱን እንቅስቃሴዎች አፈጻጸም በበላይነት መከታተል ። 1 - የፈንዱ ዋና ሥራ አስኪያጅና ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ፩ የፈንዱ ዋና ሥራ አስኪያጅና ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ በቦርዱ ይሾማሉ ። ፪ . የቦርዱ አጠቃላይ ኣመራር እንደተጠበቀ ሆኖ ፡ ዋናውሥራ አስኪያጅ የፈንዱ እንቅስቃሴዎች በፈንዱ የአፈጻጸም መመሪያ መሠረት በአግባቡ ተግባራዊ ለመሆናቸው ኃላፊ ይሆናል ። - ከላይ የተጠቀሰው አጠቃላይ ሁኔታ ሳይወሰን ዋናው ሥራ አስኪያጅ ፡ ሀ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፱ ለማዕከላዊው ጽሕፈት ቤት የተሰጠውን ሥልጣንና ተግባር ይፈጽማል ፡ ለ ) በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ መሠረት የፈንዱን ማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች ይቀጥራል ፡ ያስተዳ ደራል ፡ ሐ ) ለማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት በተፈቀደው በጀት መሠረት ክፍያዎችን ይፈጸማል ፡ መ ) በማዕከላዊው ጽሕፈት ቤት ደረጃ ከሦስተኛ ወገኖች ጋር በሚደረጉ ግንኙነቶች ሁሉ ፈንዱን ይወክላል ፡ ሠ ) የፈንዱን እንቅስቃሴዎች በብቃት ለማከናወን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሥልጣኑን ለማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች በውክልና ሊሰጥ ይችላል ። ፬ . ዋናው ሥራ አስኪያጅ በሌለበት ጊዜ ፡ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጁ ለዋናው ሥራ አስኪያጅ የተሰጠውን ተግባር ሁሉ ያከናውናል ። ክፍል ሦስት የፈንዱ የክልል አካላት ፲፩ የክልል አስተባባሪ ኮሚቴ ኣባላት እያንዳንዱ የክልል አስተባባሪ ኮሚቴ የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል : ፩ የክልል ምክር ቤት ሰብሳቢ ወይም ተወካዩ ፪ : የማኅበራዊ ልማት ዘርፍ ኃላፊ . . . . . . . . . . . . . . . ኣባል • የኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ ኃላፊ 0 የፕላንና የኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ኃላፊ . . . . ፭ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ ፮ . የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወይም የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ቅርንጫፍ ተወካይ . . . . . ፯ የሲቪክ ድርጅቶች ተወካዮች ፰ የክልሉ ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ . . አባልና ፀሐፊ ገጽ ያ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፮ የካቲት ፩ ቀን ፲፱፻ዥ፰ ዓም Federal Negarit Gazeta No . 7 13 February 1996 – Page 110 ፲፪ የክልል አስተባባሪ ኮሚቴ ሥልጣንና ተግባር እያንዳንዱ የክልል አስተባባሪ ኮሚቴ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፡ ፩ በክልሉ ውስጥ የሚካሄደው የፈንዱ እንቅስቃሴ በዚህ አዋጅ ፡ በፈንዱ የሥራ አፈጻጸም መመሪያና በቦርዱ ውሳኔዎች መሠረት መከናወኑን ያረጋግጣል ፡ ፪• የክልለ ፈንድ ጽሕፈት ቤት አዘጋጅቶ የሚያቀርበውን የክልለን ዓመታዊ የሥራ ፕሮግራምና በጀት በማጽደቅ በፈንዱ ማዕከላዊ ጽሕፈት ቤት አማካይነት ለመጨረሻ ውሳኔ ለቦርዱ ያቀርባል ፡ • የክልሉን ጽሕፈት ቤት የግማሽ ዓመትና ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸምና የፋይናንስ ሪፖርቶች ያጸድቃል ፡ ፬ ከክልሉ ፈንድ ጽሕፈት ቤት በሚቀርቡት ፕሮጀክቶች ፡ እቅዶችና በሌሎች ከፈንዱ የክልል የሥራ ፕሮግራም አፈጻጸም ጋር በተዛመዱ ነጥቦች ላይ ውሳኔ ይሰጣል ። ፲፫ የክልል አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባ ፩ የክልል አስተባባሪ ኮሚቴ በሦስት ወር አንድ ጊዜ ይሰበሰባል ። ሆኖም የኮሚቴው አስቸኳይ ስብሰባዎች | በሰብሳቢው ጥሪ በማንኛውም ጊዜ ሊደረጉ ይችላሉ ። ፪• ከኮሚቴው አባላት ከግማሽ በላይ በስብሰባው ላይ ሲገኙ ምልዐተ ጉባኤ ይኖራል ። ፫ የኮሚቴው ውሳኔ በስብሰባው ላይ በተገኙ አባላት በድምፅ ብልጫ ይሰጣል ። ድምዕ እኩል ለእኩል ከተከፈለ ሰብሳቢው ያለበት ወገን ወሳኝ ድምፅ ይኖረዋል ። ፬ ኮሚቴው የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት ደንብ ሊያወጣ ይችላል ። ፲፬ የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሥልጣንና ተግባር እያንዳንዱ የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፡ ፩ የፈንዱ እንቅስቃሴዎች በክልሉ ውስጥ እንዲሰራጩ ማድረግ ፡ ፪ የክልሉን ዓመታዊ በጀትና የሥራ ፕሮግራም አዘጋጅቶ ለክልል አስተባባሪ ኮሚቴው ማቅረብና በኮሚቴው ሲጸድቅ ለማዕከላዊው ጽሕፈት ቤት ማቅረብ ፡ ፫• በአመልካቾች የሚቀርቡ ንዑስ ፕሮጀክቶችን መገም ገምና ከውሳኔ ሃሳብ ጋር ለክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ ማቅረብ ፡ ፬• ፕሮጀክቶች ተግባራዊ የሚሆኑበትንና አስፈላጊው የአፈ ጻጸም ክትትልና ርክክብ የሚደረግበትን መንገድ ሁሉ ማዘጋጀት ፡ ፭ ለፕሮጀክቶች የተመደበውን ገንዘብ በአግባቡ በሥራ ላይ ማዋል ፡ ፮ . የግማሽ ዓመት የፋይናንስ እና የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት እያዘጋጀ ለክልሉ ኣስተባባሪ ኮሚቴማቅረብናኮሚቴው ሲያጸድቀውም ለማዕከላዊው ጽሕፈት ቤት ማቅረብ ፡ ቪ ማናቸውንም የፋይናንስና የፕሮጀክት ሬኮርድ ለማዕከ ላዊው ጽሕፈት ቤት ክፍት ማድረግ ፡ ፰ የአፈጻጸም መመሪያው በሚያዘው መሠረት የክፍያ መተኪያ ጥያቄዎችን አዘጋጅቶ ክፍያ እንዲፈጸም ለማዕከላዊው ጽሕፈት ቤት ማቅረብ ። _ ፲፭ የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ ፩ እያንዳንዱ የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሥራ አስኪያጅ በክልሉ አስተባባሪ ኮሚቴ ይሾማል ። ገጽ ፲፩ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፯ የካቲት ፭ ቀን ፲፱ደተቛ ዓም : Federal Negarit Gazeta – No . 7 - 13 February 1996 - Page 111 ፪ በአስተባባሪው ኮሚቴ የሚሰጠው አጠቃላይ መመሪያ እንደተጠበቀ ሆኖ ፡ ሥራ አስኪያጁ የፈንዱ እንቅስቃ ሴዎች በፈንዱ የአፈጻጸም መመሪያ መሠረት በአግባቡ ተግባራዊ ለመሆናቸውኃላፊ ይሆናል ። ፫ . ከላይ የተጠቀሰው አጠቃላይ ሁኔታ ሳይወሰን ሥራ አስኪያጁ ፤ ሀ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፬ ለክልሉ ፈንድ ጽሕፈት ቤት የተሰጠውን ሥልጣንና ተግባር ይፈጽማል ! ለ ) በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ መሠረት የክልሉን ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች ይቀጥራል ያስተዳድራል ፤ ሐ ) ለክልሉ ፈንድ ጽሕፈት ቤት በተፈቀደው በጀት መሠረት ክፍያዎችን ይፈጽማል ፤ መ ) በክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት ደረጃ ከሦስተኛ ወገኖች ጋር በሚደረጉ ግንኙነቶች ሁሉ ፈንዱን ይወክላል ፣ ሠ ) በክልሉ የፈንዱን እንቅስቃሴዎች በብቃት ለማከ ናወን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ሥልጣኑን ለክልሉ ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች በውክልና ሊሰጥ ይችላል ። ክፍል አራት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ፲፮ . የአሠራር ወጥነትን ስለማረጋገጥ የፈንዱን የአሠራር ወጥነት ለማረጋገጥ የሥራ አፈጻጸም መመሪያው የፈንዱን አጠቃላይ ተግባራትና እንቅስቃሴዎች | የሚገዛ ይሆናል ። ፲፯ በጀት ፩• የፈንዱ በጀትከፌዴራሉ መንግሥት ፡ ከለጋሽ ድርጅቶችና ከሕብረተሰቡ የሚደረግ የገንዘብ መዋጮና ከዓለም ባንክ የሚገኝ ብድር ይሆናል ። ፪• ከክልሎች ፡ ከፌዴራሉ መንግሥትና ከለጋሽ ድርጅቶች የሚሰጡ ቢሮዎች ፡ መሣሪያዎች ፡ ዕቃዎችና የመሳሰሉት ለፈንዱ ተጨማሪ ገቢዎች ሊሆኑ ይችላሉ ። ፫• በጀቱ የገንዘብ መዋጮዎቹ ከተደረጉበት የብድርና ዕርዳታ ስምምነቶች ጋር በተጣጣመ መልኩ ተግባራዊ ይሆናል ። ፲፰ የባንክ ሂሣብ ፩ . በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፯ ( ፩ ) የተጠቀሰውመዋጮ በፈንዱ ስም በባንክ ተቀማጭ ይሆናል ። ፪• ማዕከላዊው ጽሕፈት ቤት የሚከተሉት የባንክ ሂሳቦች ይኖሩታል ፤ ሀ ) የውጭ ምንዛሪ ሂሣብ ፡ ከውጭ ዕርዳታና ብድር ሰጪዎች ለሚገኘው ገንዘብ ፤ ለ ) የብር ( የአገር ውስጥ ገንዘብ ) ሂሳብ ። የክልል ፈንድ ጽሕፈት ቤት ሁለት የተለያዩ የአገር ውስጥ ገንዘብ የባንክ ሂሳቦች ለሁለት የተለያዩ ጉዳዮች ይኖሩታል ፤ ሀ ) ለንዑስ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ ፡ እና ለ ) ለሥራ ማስኬጃ ፡ የሚውል ። ፲፱ ኦዲት የፈንዱ ሂሣብ በየዓመቱ በውጭ ኦዲተሮች ይመረመራል ። ፳ : የዕቃ ግዥና አጠቃቀም በፈንዱ የሥራ አፈጻጸም መመሪያ ውስጥ በተመለከተው መሠረት ፈንዱ የራሱ የዕቃ ግዥና አጠቃቀም ሥርዓት ይኖረዋል ። ገጽ ፻፲፪ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፪ የካቲት ፭ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ . ም . Federal Negarit Gazeta No . 7 13 February 1996 – Page 112 ፳፩• የመብትና ግዴታ መተላለፍ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶ ፈንድ መብትና ግዴታ በዚህ | አዋጅ ለፈንዱ ተላልፋል ። ፳፪• የመተባበር ግዴታ ማንኛውም ግለሰብ ፥ የመንግሥት አካላትና የግል ድርጅቶች ፈንዱ ሥራውን በሚያከናውንበት ጊዜ የመተባበር ግዴታ አለባቸው ። ፳፫• አዋጁ የሚጸናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከየካቲት ፭ ቀን ፲፱፻T፰ ዓም ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ የካቲት ፭ ቀን ፲፱፻ዥ፰ ዓም ዶ / ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?