የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ሰባተኛ ዓመት ቁጥር 70 አዲስ አበባ ጥር ፳፪ ቀን ፲ህየን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፪፻ወ፩ በህየን ዓ - ም ለሴቶች ልማት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ከዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር ብድር ለማግኘት የተፈረመው የብድር ስምምነት ማዕደቂያ አዋጅ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፩ ፲፱፻፲ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለምአቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረገውን የብድር ስምምነት ለማፅደቅ የወጣ አዋጅ ለሴቶች ልማት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል መጠኑ ኤስዲ - አር / ሚሊዮን ፳የሺህ ( ሦስት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺ ኤስዲ - አር ) የሆነ ገንዘብ የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለም አቀፍ የልማትማኅበር መካከል እ.ኤ.አ. ኦገስት ፳፯ ቀን ፪ሺ በዋሽንግተን ዲሲ የተፈረመ በመሆኑ፡ መሠረታዊ የኤኮኖሚ ዓለምአቀፍ ውሎች ተፈፃሚ ከመሆናቸው በፊት መጽደቅ ስላለባቸው፡ ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥር ፳፪ ቀን ፲፱የን ! ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው ስለሆነ፡ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፶፭ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እና ( ፪ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ ለሴቶች ልማት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ከዓለም አቀፍ የልማትማኅበር ብድር ለማግኘት የተፈረመው የብድር ስምምነት ማዕደቂያ አዋጅ ቁጥር ፪፻ወ፩ 1 ህየን ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ . ትርጓሜ በዚህ አዋጅ ውስጥ “ የብድር ስምምነት ” ማለት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል እ.ኤ.አ ኦገስት ፳፰ ቀን ፪ሺ በዋሽንግተን ዲሲ የተፈረመው ቁጥር ፫ሺ፱የጊ ኢት • የብድር ስምምነት ነው ። ያንዱ ዋጋ ብር 2:30 ነጋሪት ጋዜጣ ፖ.ሣ.ቁ : ዥሺ፩ ፌደራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር 18 ጥር ፳፪ ቀን ፲ህየ ፣ ዓ • ም • የገንዘብ ሚኒስትር ሥልጣን የገንዘብ ሚኒስትሩ በብድር ስምምነቱ የተገኘውን ኤስዲ - ኣር ፤ ሚሊዮን ፫፻ሺህ ( ሦስት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሺህ ኤስዲ - ኣር ) በብድር ስምምነቱ በተመለከቱት ሁኔታዎች መሠረት በሥራ ላይ እንዲውል ለማድረግ በዚህ አዋጅ ሥልጣን ተሰጥቶታል ። ፬ አዋጁ የሚጸናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከጥር ፳፪ ቀን ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ ጥር ፳፪ ቀን ፲፱፻፵፫ ዓም ዶ ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ