×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
አዋጅ ቁጥር ፫፻፳፩/፲፱፻፲፭ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ኣዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ° ማሻሻያ ) ► የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ዘጠነኛ ዓመት ቁጥር ፵፩ አዲስ ኣበባ - መጋቢት ፴ ቀን ፲፱፻፲፭ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፫፻፳፩ / ፲፱፻፲፭ ዓም የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ኣዋጅን ለማሻሻል የወጣ ገጸ ፪ሺ፩፻፴ አዋጅ ቁጥር ፫፻፳፩ / ፲፱፻፲፭ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅን ለማሻሻል የወጣ አዋጅ የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን ኣዋጅ ቁጥር ፳፭ / ፲፱፻፰ እንደተ ሻሻለ እንደገና ማሻሻል በማስፈለጉ ፤ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፶፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ፩ ) አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ቁጥር ፫፻፳፩ / ፲፱፻፲፭ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ ) ማሻሻያ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር ፳፭ / ፲፱፻ዥ፰ እንደሚከ | 2. Amendment ተለው ተሻሽሏል ። ፩ . የአንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ተሠርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ተተክቷል ። “ ፩ . በመንግሥት ግዛት ሀገር ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች፡ ” ፪ . የአንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) ተሠርዞ በሚከተለው አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ተተክቷል ፤ “ ፱ ዓለም አቀፍ የዲፕሎማቲክ ሕጎችና ልምዶች እንዲሁም ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው ሌሎች ዓለም አቀፍ ስምምነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ፤ ልዩ መብትና ጥበቃ ያላቸው በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ የውጭ ሀገር ሰዎች ተበዳይ ወይም ተከሳሽ የሆኑባቸው ወንጀሎች ፡ እንዲሁም የዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፪ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) እና እንቀጽ ፲፭ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ከ፭ ዓመት ጽኑ እሥራት በላይ ሊያስቀጡ የሚችሉ የውጭ ሀገር ዜጎች ተበዳይ ወይም ተከሳሽ የሆኑባቸው ወንጀሎች፡ ” ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ ሺ፩ ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፩ መጋቢት ፴ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ.ም በአንቀጽ ፪ ሥር የሚከተሉት አዲስ ንዑስ አንቀጽ ( ፲፫ ) እና ( ፲፬ ) ተጨምረዋል ፣ “ ፲፫ ) በተለያዩ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦች፡ ጎሣዎች ፡ በሃይማኖት ተከታዮች ወይም በፖለቲካ ቡድኖች መካከል ከተፈጠረ ግጭት ጋር የተያያዙ ወንጀሎች ፤ ፲፬ ) በፌዴራል መንግሥቱ ንብረቶች ላይ በሚፈጸሙ እና የዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፪ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) እና አንቀጽ ፲፭ ንዑስ አንቀጽ ( ፫ ) እንደተጠበቀ ሆኖ፡ ከ፭ ዓመት ጽኑ እሥራት በላይ ሊያስቀጡ የሚችሉ ወንጀሎች፡ ” ፬ ) የአንቀጽ ፲፪ ተሠርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀጽ ፲፪ | 4 ) Article 12 is deleted and replaced by the following new ተተክቷል ፣ “ ፲፪ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የመጀመሪያ ደረጃ የወንጀል የዳኝነት ሥልጣን የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ሥልጣን ይኖረዋል፡ ፩ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ፡ ( ፪ ) ( ፫ ) ፡ ( ፰ ) ፡ ( ፬ ) እና ( ፲፫ ) በተመለከቱት የወንጀል ጉዳዮች፡ ፪ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) የውጭ ሀገር ዜጎችን እንዲሁም አንቀጸ ( 10 ) ን በሚመለ ከቱና በሥራ ላይ ባሉት ሕጎች ለከፍተኛ ፍርጅ ቤት በተሰጡ የወንጀል ጉዳዮች፡ ፫ ) በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተሞች ውስጥ በሚነሱና በሥራ ላይ ባሉ ሌሎች ሕጎች ለከፍተኛ ፍርድ ቤት በተሰጡ በሌሎች የወንጀል ጉዳዮች ። ” ፭ አንቀጽ ፲፭ ተሠርዞ በሚከተለው አዲስ አንቀጽ ፲፭ ተተክቷል ፤ “ ፲፭ . የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የወንጀል የዳኝነት ሥልጣን የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በሚከተሉት የወንጀል ጉዳዮች ላይ የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ሥልጣን ይኖረዋል፡ ፩ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) ፡ ( ፭ ) ፡ ( ፩ ) እና ( ፯ ) በተመለከቱት የወንጀል ጉዳዮች፡ ፪ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) የውጪ ሀገር ዜጎችን እንዲሁም ንዑስ አንቀጽ ( ፲፬ ) ን በሚመ ለከቱና በሥራ ላይ ባሉት ሕጎች ለወረዳና ለአውራጃ ፍርድ ቤት በተሰጡ የወንጀል ጉዳዮች፡ ፫ ) በሕግ ለሌሎች ኣካላት የተሰጠው የዳኝነት ሥልጣን እንደተጠበቀ ሆኖ ፤ በአዲስ አበባ እና ደሬዳዋ ከተሞች ውስጥ በሚነሱና በሥራ ላይ ባሉ ሌሎች ሕጎች ለወረዳና ለአውራጃ ፍርድ ቤቶች በተሰጡ በሌሎች የወንጀል ጉዳዮች ። ” በክልል ፍርድ ቤቶች በመታየት ላይ ስላሉ ጉዳዮች ይህ አዋጅ ከመፅናቱ በፊት በክልል ፍርድ ቤቶች በመታየት | 7 . Effective Date ላይ ያሉ በዚህ አዋጅ የተሻሻለውን ኣንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ፡ ( ፱ ) ፡ ( ፲፫ ) ኣና ( ፲፬ ) የሚመለከቱ፡ የወንጀል ጉዳዮች ሥልጣን ወደአላቸው ፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተዛውረው ይታያሉ ። ፯ አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከመጋቢት ፴ ቀን ፲፱፻፲፭ ዓም ጀምሮ የፀና ይሆናል ። አዲስ አበባ መጋቢት ፴ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ.ም ግርማ ወልደጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?