×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 19/1989 ዓ•ም• የመገናኛ ብዙኃን ማሠልጠኛ ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

| ኣዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፳፯ አንቀጽ ፭ መሠረት'ቲትዩት ማቋቋ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ሦስተኛ ዓመት ቁጥር ፶፭ አዲስ አበባ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፷፱ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፲፱ / ፲፱፻፷፱ ዓም የመገናኛ ብዙኃን ማሠልጠኛ ኢንስቲትዩት ማቋቋሚያ የሚኒስ ትሮች ምክር ቤት ደንብ ገጽ ፮፻፴፪ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፲፱ / ፲፱፻፳፬ የመገናኛ ብዙኃን ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩትን ለማቋቋም የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው ደንብ አውጥቷል ። ፩ . አጭር ርዕስ ይህ ደንብ “ የመገናኛ ብዙኃን ማሠልጠኛ ሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር ፲፬ / ፲፱፻፲፬ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ . ትርጓሜ “ ሚኒስትር ” ማለት የማስታወቂያና ባህል ሚኒስትር ነው ። ፫ መቋቋም ፩ . “ የመገናኛ ብዙኃን ማሠልጠኛ ኢንስቲትዩት ( ከዚህ በኋላ “ ኢንስቲትዩቱ ” ተብሎ የሚጠራ ) እራሱን የቻለ የሕግ ሰውነት ያለው የሥልጠና ተቋም በዚህ ደንብ ተቋቁሟል ። ፪ ኢንስቲትዩቱ ተጠሪነቱ ለሚኒስትሩ ይሆናል ። ኢንስቲትዩቱ የሚከተሉት ዓላማዎች ይኖሩታል ፡ ፩ የኢት : ጵያ ሕዝቦች ማኅበራዊ ፣ ባሕላዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እንዲፋጠን ፡ ነፃ ፡ ዲሞክራሲያዊና በቂ መረጃ የሚያገኝ ኅብረተሰብ እንዲፈጠር ንቁና ገንቢ ሚናን የሚጫ ወት የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያ ማፍራት : ባለሙያው ይኸንን ተግባር በብቃትና በተሟላ መልኩ ገቢራዊ እንዲያደ ርገው የሚያስችል ሙያን ማስጨበጥ ፤ ያንዱ ዋ ? 340 ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ ፰ሺ፩ ገጽ ፭፻፴፫ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፭ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓም ከብሔር ፡ ከዘር ፣ ከቋንቋ : ከሃይማኖትና ከሌሎች አድልዎች ነጻ የሆነ ፣ የመከባበርን ፡ የመተማመንን ፡ የመተሳሰብንና የመቻቻልን ባሕል የሚያጎለብት ፣ ሁለንተናዊ ሰብዕናን የሚያበለጽግ የሰውን ልጅ ክቡርነት የሚያጠናክር ትምህርት መስጠትና ባለሙያን መቅረጽ ፤ የኢትዮጵያን ሕዝቦች ባሕልና ታሪክ የሚያውቅ ከሕዝቦች ጋር ግልጽ ፣ ነጻና ዲሞክራሲያዊ ግንኙነት የሚኖረው የመገናኛ ብዙኃን ሰው እንዲፈጠር የሚያዘጋጅና የሚያበቃ ሙያዊ ትምህርት መስጠት ፣ ፬ የጋዜጠኛውና ባጠቃላይም የመገናኛ ብዙኃን ሠራተኞች ሁለገብ እውቀትእንዲዳብር ፤ የጋዜጠኝነት ሙያ እንዲደረጅ የሙያ ሥነ ምግባር እንዲከበር ፤ የሥራ ክቡርነትእንዲታወቅ ፈር የሚያስይዝ ትምህርት እንዲሰጥ ማድረግ ፤ በልዩ ልዩ የመገናኛ ብዙኃን መስኮች ጥናትና ምርምር ማካሄድና ጠቃሚ ውጤቶችን ማሠራጨት ። ፭ . የኢንስቲትዩቱ ሥልጣንና ተግባር ኢንስቲትዩቱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ የሀገሪቱን የትምህርት መሠረታዊ ፖሊሲ በመከተል መንግ ሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ለሚሠሩ ጋዜጠኞ ችና ለሌሎች የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ፣ እንዲሁም ለአዳዲስ ተማሪዎች የጋዜጠኝነት ሙያ ሥልጠና ይሰጣል ፣ ፪ ዲፕሎማና የምስክር ወረቀት ይሰጣል ፣ ፫ ሴሚናሮች ፡ ወርክሾፖችና ሲምፖዚየሞች ያዘጋጃል ፣ ያካሂ በሀገር ውስጥና በሌሎች ሀገሮች ከሚገኙ አቻ ተቋማትና ተመሣሣይ ዓላማ ካላቸው አካላት ጋር ግንኙነት ይመሠር ታል ፡ የሥራ ዝምድና ይፈጥራል : ፭ የኢንስቲትዩቱን የማሠልጠን አቅምና የብቃት መመዘኛ ዘዴዎቹን በተመለከተ መመሪያ ያወጣል ፤ ፮ ኢንስቲትዩቱ ስለሚስፋፋበትና በተስማሚ ቴክኖሎጂና በሠ ለጠነ የሰው ኃይል ስለሚደራጅበት ሁኔታ በማጥናት ተግባ ራዊ ያደርጋል ፡ ፯ ለሚሰጠው አገልግሎት በከፊል ወይም በሙሉ ክፍያ ሊያስከ ፍል ይችላል ፣ የንብረት ባለቤት ይሆናል ፡ ውል ይዋዋላል ፣ በስሙ ይከሳል ፣ ይከሰሳል ፡ ፬ . ዓላማውን ከግብ ለማድረስ የሚያስችሉ ሌሎች ተግባሮችን ያከናውናል ። ፮- የኢንስቲትዩቱ አቋም ኢንስቲትዩቱ ፡ ፩ ቦርድ ፡ ፪ . ዳሬክተር እና ምክትል ዳሬክተር ፡ ፫ • ኣካዳሚክ ካውንስል ፡ እና ፬ • አስፈላጊው ሠራተኞች ይኖሩታል ። ፯ : የቦርዱ አባላት ፩ ኢንስቲትዩቱ ፯ ( ሰባት ) ኣባላት ያሉት ቦርድ ይኖረዋል ። የቦርዱ አባላት አግባብ ካላቸው ተቋሞችና ከልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በሚኒስትሩ ይሰየማሉ ። የቦርዱ ሥልጣንና ተግባር ቦርዱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፡ ፩ ኢንስቲትዩቱ በዓላማው መሠረት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማድረጉን ያረጋግጣል ፡ ጀ የአስተዳደር ፖሊሲ ያመነጫል ፡ በሚኒስትሩ ሲፀድቅም ተግባራዊ መሆኑን ያረጋግጣል ፡ ቦርዱ ዝርዝር የስብሰባ ሥነ ሥርዓት 0 . ገጽ ፭፻፴፬ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፭ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. ፫ የኢንስቲትዩቱን የአካዳሚክ ፖሊሲ ያፀድቃል ፡ ፬ . ኢንስቲትዩቱ የሚተዳደርበትን መመሪያ አዘጋጅቶ ለሚኒስ ትሩ አቅርቦ ያስጸድቃል ፡ ሲፈቀድም ተግባራዊ መሆኑን ያረጋግጣል ፡ ፭ የኢንስቲቱዩቱን አደረጃጀት ይወስናል ፡ ኢንስቲትዩቱ የሚስፋፋበትን ፡ የሚጠናክርበትንና አሠራሩ የሚሻሻልበ ትን መንገድ ይቀይሳል ፡ ፮ . የኢንስቲትዩቱን ዳሬክተርና ም / ዳሬከተር ይሾማል ፡ ፯ በኢንስቲትዩቱ በማስተማር ወይም በምርምር እንዲሁም በፕሮዳክሽንና በኢንጂነሪንግ ተግባር ላይ የተሰማሩ የአካዳ ሚክ ሠራተኞች የሚቀጠሩበትንና የሚተዳደሩበትን መመ ሪያ ያወጣል ፡ ፰ የኢንስቲትዩቱን ዕቅድና ረቂቅ በጀት ለሚኒስትሩያቀርባል፡ ፱- የኢንስቲትዩቱ መለያ ምልክት የሚሆነውን ዓርማ ይወስ ፲ . ኢንስቲትዩቱ የሚያስከፍላቸውን ክፍያዎች ይወስናል ፡ ፲፩ . የኢንስቲትዩቱ ተማሪዎችና ሠልጣኞች አቀባበልን መመሪያ ያወጣል ፡ ፲፪ • ኢንስቲትዩቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር አቻ ተቋማትና ከሌሎች ጋር የሚያደርጋቸውን ስምምነቶች መርምሮ ያፀድ የቦርዱ ስብሰባ ቦርዱ በወር አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል ። ፪ አስቸኳይ ሁኔታ ሲያጋጥም በቦርዱ ሰብሳቢ ጥሪ ወይም ከቦርዱ አባላት መካከል ቢያንስ ሁለት አባላት ሲጠይቁ በማናቸውም ጊዜ ሊሰበሰብ ይችላል ፡ በስብሰባው ላይ ከግማሽ በላይ አባላት ከተገኙ ምልዓተ ጉባዔ ይሆናል ። ቦርዱ ውሣኔ የሚያስተላልፈው በድምጽ ብልጫ ይሆናል ። ድምጽ እኩል በኩል የተከፈለ እንደሆነ ሰብሳቢው ያለበት ወገን ሀሳብ የቦርዱ ውሳኔ ይሆናል ። ፭ ከዚህ በላይ የተመለከቱት ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆኖ : ለማውጣት ይችላል ። ቦርዱ የራሱ ፀሐፊ ይኖረዋል ። ፬ ስለ ኢንስቲትዩቱ ዳሬክተር ሥልጣንና ተግባር ዳሬክተሩ የኢንስቲትዩቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ከቦርዱ በሚሰጠው አጠቃላይ መመሪያ መሠረት የኢንስቲት ዩቱን ሥራ ይመራል ፡ ያስተዳድራል ። በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) የተመለከተው አጠቃላይ አገላለጽ እንደተጠበቀ ሆኖ ዳሬክተሩ : ሀ ) ለኢንስቲትዩቱ የተሰጡትን ሥልጣንና ተግባሮች ሥራ ላይ ያውላል ፡ ለ ) የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ መርሆዎችን ተከትሎ ቦርዱ በሚያወጣው መመሪያ መሠረት በኢንስትቲዩቱ ውስጥ በማስተማር ፡ በማሠልጠን ወይም በምርምር ተግባር ላይ የተሠማሩ የአካዳሚክ ፡ የኢንጂነሪንግና የፕሮዳክሽን ሠራተኞችን ይቀጥራል ፡ ያስተዳድራል ፡ ደሞዝና አበላቸውን በቦርዱ ውሣኔ መሠረት ያስፈጽ ማል ፡ ሌሎች ሠራተኞችን በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ መሠረት ይቀጥራል ያስተዳድራል : ሐ ) የኢንስቲትዩቱን ዓመታዊ የሥራ ፕሮግራምና ረቂቅ በጀት ለቦርዱ ያቀርባል ፡ ሲፈቀድም በሥራ ላይ ያውላል ፣ = ጽ ፮፻፴፭ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፭ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፷፱ ዓም : በቦርዱ ሲፈቀድ በኢንስቲትዩቱ ሥም ማናቸውንም ውሎች ይዋዋላል ፡ ኢንስቲትዩቱን በሶስተኛ ወገኖች ዘንድ ይወክላል ፤ ረ ) ለኢንስቲትዩቱ በተፈቀደው በጀትና ፣ የሥራ ፕሮግራም መሠረት ገንዘብ ወጪ ያደርጋል ፡ በኢንስቲትዩቱ ስም የባንክ ሂሣብ ይከፍታል ፡ ያንቀሳቅሳል ፤ ሰ ) በየሶስት ወሩ ስለኢንስቲትዩቱ የሥራ እንቅስቃሴ ለቦ ርዱ ሪፖርት ያቀርባል ፡ ሸ ) በቦርዱ ስብሰባዎች ላይ በአስረጅነት ይገኛል ፤ በቦርዱ የሚሰጡትን ሌሎች ተግባሮች ያከናውናል ። ዳሬክተሩ ለኢንስቲትዩቱ ሥራ ቅልጥፍና በሚያስፈልግ መጠን ሥልጣንና ተግባሩን በከፊል ለኢንስቲትዩቱ ፡ ሌሎች ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሊያስተላልፍ ይችላል ። ፲፩ . ስለኢንስቲትዩቱ ምክትል ዳሬክተር ፩ . የኢንስቲትዩቱ ዳሬክተር በማይኖርበት ጊዜ ምዳሬክተሩ ፣ ዳይሬክተሩን ተክቶ የኢንስቲትዩቱን ሥራ ይመራል ፣ ያስተባብራል ፡ በዳሬክተሩተለይተው የሚሰጡትን ሥራዎች ያከናውናል ። ፲፪ ስለአካዳሚክ ካውንስል ኢንስቲትዩቱ በቦርዱ የሚሰየሙ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አባላት የያዘ የአካዳሚክ ካውንስል ይኖረዋል ፣ ፩ . የኢንስቲትዩቱ ዳሬክተር ፪ የኢንስቲትዩቱ ም ዳሬክተር . ፫ ሬጅስትራር . ፬- በኢንስቲትዩቱ ተማሪዎች የሚመረጥ አንድ የተማሪዎች ተወካይ . በኢንስቲትዩቱ ቋሚ መምህራን የሚመረጥ አንድ የመምህራን ተወካይ .. በቦርድ የሚመረጡ ከሦስት የማይበልጡ የፋካሊቲ አባሎች ... የአካዳሚክ ካውንስሉ ሥልጣንና ተግባር የአካዳሚክ ካውንስሉ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩ ፩ የኢንስቲትዩቱን ልዩ ልዩ የትምህርት ፕሮግራሞችና ካሌን ደር መርምሮ ለቦርድ ያቀርባል ፡ ፪ : ዲፕሎማ : ሠርተፊኬትና ልዩ ሽልማት ስለሚሰጥበት ሁኔታ ለቦርዱ የውሣኔ ሀሳብ ያቀርባል ፣ ፫ የተማሪዎችና ሠልጣኞች አቀባበልን ፡ የትምህርት ደረጃ አወሳሰንን ፡ ምዘናን የዲሲፕሊንና የምረቃ ጉዳዮችን የሚመለከቱ መመዘኛ መስፈርቶችን አዘጋጅቶ ለቦርዱ ያቀርባል ፡ ሲፈቀድም ተግባራዊ ያደርጋል፡ በነዚህ ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ አቤቱታዎችንና ቅሬታዎችን መርምሮ ውሣኔ ይሰጣል ፡ አጠቃላይ የፈተና አሰጣጥ ዘዴና ሁኔታን ይወስናል ፤ ፭ ስለአካዳሚክ ዕድገቶች ጉዳይ አጥንቶ ለቦርዱ በማቅረብ ያስወስናል ፡ ፲ ወደሚቀጥለውየትምህርት እርከን የሚሸጋገሩተማሪዎችን ዝርዝር መርምሮ ይወስናል ፡ የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት ደንብ ያወጣል ፤ ፰ በቦርዱ የሚሰጡትን ሌሎች ተግባሮች ያከናውናል ። የኢንስቲትዩቱ በጀት ከሚከተሉት ምንጮች የተውጣጣ ይሆ ፩ . በፌዴራል መንግሥት ከሚመደብለት በጀት ፤ ጀ ኢንስቲትዩቱ ከሚያገኛቸው የአገልግሎት ክፍያዎች እና ፫ • ከሌሎች ምንጮች ። ገጽ ፮፻፴፭ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፭ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓም ፲፭ የሂሣብ መዛግብት ፩ ኢንስቲትዩቱ የተሟሉና ትክክለኛ የሆኑ የሂሣብ መዛግብ ትና ሰነዶችን ይይዛል ። ፪ • የኢንስቲትዩቱ የሂሣብ መዛግብትና ሰነዶች በዋናው ኦዲ ተር ወይም እርሱ በሚሰይማቸው ሌሎች ኦዲተሮች በየአ መቱ ይመረመራሉ ። ደንቡ የሚጸናበት ጊዜ ይህ ደንብ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ ነሐሴ ፴ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓም መለስ ዜናዊ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?