×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
አዋጅ ቁጥር 161 1991 የኢትዮ ማሌዥያ የንግድ ስምምነት ማጽደቂያ አዋጅ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ አምስተኛ ዓመት ቁጥር ፵፪ አዲስ አበባ የካቲት ፳፭ ቀን ፲፱፻፲፩ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፩፻፷፮ / ፲፱፻፶፩ ዓ.ም የኢትዮ ማሌዥያ የንግድ ስምምነት ማጽደቂያ ገፅ ፩ሺህ፮ አዋጅ ቁጥር ፩፻፷፮ / ፲፱፻፲፩ የኢትዮ ማሌዥያ የንግድ ስምምነትን ለማጽደቅ የወጣ አዋጅ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በማሌዥያ መንግሥት መካከል የተደረገው የንግድ ስምምነት ጥቅምት ፲፪ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ ም • ኩዋላ ላምፑር ላይ የተፈረመ ስለሆነ ፤ ስምምነቱ በሥራ ላይ የሚውለው በተዋዋዮቹ ሀገሮች ከተፈ ረመና በየሕጐቻቸው መሠረትም መሟላት ያለባቸው ሕጋዊ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ከተገላለጹ በኋላ እንደሚሆን በስምምነቱ ውስጥ ስለተመለከተ ፣ ይህንኑ ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የተወካዮች ምክር ቤት የካቲት ፳፭ ቀን ፲፱፻፵፩ ዓም ባደረገው ስብሰባ ያጸደቀው ስለሆነ ፣ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፲፩ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እና ( ፲፪ መሠረት ከዚህ እንደሚከተለው ታውጇል ። ፩ . አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የኢትዮ ማሌዥያየንግድ ስምምነት ማጽደቂያ አዋጅ ቁጥር ፩፻፷፮ / ፲፱፻፲፩ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ ስምምነቱ ስለመጽደቁ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በማሌዥያ መንግሥት መካከል ጥቅምት ፲፪ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓም ኩዋላ ላምፑር ላይ የተፈረመው የንግድ ስምምነት ጸድቋል ። ያንዱ ዋጋ ብር 230 ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ ፰ሺ፩ ገጽ ፩ሺህ፯ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፪ የካቲት ፳፭ ቀን ፲፱፻፶፩ ዓም ፫ • የአስፈጻሚው አካል ሥልጣን ይህ ስምምነት በሥራ ላይ እንዲውል የማድረግ ሥልጣን ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በዚህ አዋጅ ተሰጥቶታል ። ፬ አዋጁ የሚጸናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከየካቲት ፳፭ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ የካቲት ፳፭ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓም : ዶ / ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?