የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ አራተኛ ዓመት ቁጥር ፴፭ አዲስ ኣበባ - ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፲ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፩፻፲፯ / ፲፱፻፲ ዓም የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ገበያ ልማት ባለሥልጣን | Animal , Animal Products and By - products Marketing ማቋቋሚያ አዋጅ . . . . . . . . . . . ገጽ ፯፻፳፩ አዋጅ ቁጥር ፩፻፲፯ / ፲፱፻፲ የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ገበያ ልማት ባለሥልጣንን “ ለማቋቋም የወጣ አዋጅ . እንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ውስጥ ከፍተኛ ሚና ያለው የግብርና ሀብት በመሆኑ ፡ የዚህንም ሀብት አቅርቦትና ግብይት ሥርዓት በተገቢው | are agricultural resources having an important role in the መንገድ በመምራት ፡ በመቆጣጠርና በማስተባበር ሀገሪቱ ልታገኝ | economy of the country , የምትችለውን ጥቅም ማሳደግ በማስፈለጉ ፡ : በእንስሳት ፡ እንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች መረጃና ድጋፍ መስጠት እንዲሁም የገበያ ሁኔታን ማመቻቸት አስፈላጊ በመሆኑ ፡ . እስከአሁን ድረስ ባለቤት አጥቶ በተበታተነ ሁኔታ ሲከናወን የነበረውን የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ የውጭ አገር ገበያ አቅርቦት ሁኔታዎችን በተመለከተ በሥራዎቹ ልዩ ባህርይ | thereof : . ምክንያት በሌላ መሥሪያ ቤት እንዲካሄዱ የግድ አስፈላጊ ከሆኑት አገልግሎቶች በስተቀር ለአፈጸጸም በሚያመችና በተጠቃለለ መልክ መከናወን እንዳለበት ስለታመነበት ፣ ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ ራሱን የቻለና ሥራዎቹን በባለቤትነት የሚመራ አስፈላጊው ሥልጣንና ተግባር ያለው የመንግሥት መሥሪያ ቤት ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፣ ያንዱ ዋጋ 340 . ነጋሪት ጋዜጣ ፖሣቁ ዝሸ፩ ገጽ ፯፻፳፪ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፭ ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፶ ዓም በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመን ግሥት አንቀጽ ፲፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ፩ . አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትናተዋጽኦ ገበያ ልማት ባለሥልጣን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር ፩፻፲፯ ፲፱፻፶ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ አዋጅ ውስጥ ፡ ፩ “ እንስሳት ” ማለት የዳልጋ ከብት ፥ በግ ፥ ፍየል ፥ ግመል ፡ ዶሮ ፡ አሳማ ፡ ንብና ባለሥልጣኑ ወደፊት ለዚህ አዋጅ ዓላማ እንስሳት ብሎ የሚሰይማቸውን ሁሉ ያጠቃልላል ፤ “ የእንስሳት ምርት ” ማለት ሥጋ ፡ ወተት ፡ ቅቤ ፡ አይብ ፥ እንቁላል ፡ ማር ፡ ሰም ፡ የበግ ፀጉርና ሱፍ ፡ ባለሥልጣኑ ወደፊት የእንስሳት ምርት ብሎ የሚሰይማቸውን ያጠቃ ፫ . “ የእንስሳት ተዋጽኦ ” ማለት ከእንስሳት እርድ የሚገኙ ተረፈውጤቶች ፡ እንደ ቆዳ ፡ ሌጦ ፥ ቀንድ ፡ ሸኮና ፡ ከሥጋ ደምና አጥንት የተሠራ መኖ እንዲሁም ባለሥልጣኑ ወደፊት የእንስሳት ተዋጽኦ ብሎ የሚሰይማቸውን ያጠቃ ፬ . “ ኳራንቲን ” ማለት የተለያዩ ተላላፊና በካይ የእንስሳት በሽታዎች በሀገር ውስጥ ከቦታ ወደቦታ ፡ ከሀገር ውስጥ ወደ ውጭ ፡ ከውጭም ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይዛመቱ ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል አሠራር ነው ፡ ፭ “ የኳራንቲን ጣቢያ ” ማለት በአንድበተወሰነና በተከለለ ቦታ እንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ላይ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር የሚደረግበት ቦታ ነው ፡ ፮ . “ የማረፊያ ቦታ ” ማለት የእንስሳት ንግድ የጉዞ አቅጣጫን ተከትሎ ለእንስሳቱ የውኃ ፡ የመኖ ፡ የጤናና የማረፊያ አገልግሎት ለመስጠት በተወሰነ ርቀት የሚቋቋም የተከለለ ቦታ ነው ። ፯ . “ የአገልግሎት ክፍያ ” ማለት ባለሥልጣኑ ለሚሰጠው ማናቸውም አገልግሎት ወደፊት በሚወጣ ደንብ መሠረት ተወስኖ የሚከፈል ገንዘብ ነው ፣ ፰ “ ክልል ” ማለት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመንግሥት አንቀጽ ፵፯ ( ፩ ) ላይ የተመለከ | ቱትን ማለት ሲሆን ለዚህ አዋጅ አፈጻጸም ሲባል የአዲስ | 3 . Establishment ! " አበባና የድሬዳዋ አስተዳደርንም ይጨምራል ። ፫ መቋቋም የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ባለሥልጣን ( ከዚህ በኋላ “ ባለሥልጣኑ ” እየተባለ የሚጠራ ) የሕግ | ሰውነት ያለው ራሱን የቻለ የፌዴራል የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሆኖ በዚህ አዋጅ ተቋቁሟል ። • የባለሥልጣኑ ተጠሪነት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሆናል ። | a ፬ . ዋና መሥሪያ ቤት የባለሥልጣኑ ዋና መሥሪያ ቤት አዲስ አበባ ሆኖእንደአስፈላ | ጊነቱ በክልሎች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ሊኖሩት ይችላል ። | ባለሥልጣኑ የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ገበያ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር እንዲስፋፋ ኣቅርቦቱ በመጠንና በጥራት እንዲያድግ የማድረግ ዓላማ ይኖረዋል ። ገጽ ፯፻፳፫ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፴፭ ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፲ ዓ . ም . . . ፮ . የባለሥልጣኑ ሥልጣንና ተግባር ባለሥልጣኑ የሚከተለው ሥልጣንና ተግባር ይኖረዋል ፡ ፩ የሀገሪቱን የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ገበያ ለማስፋፋት የሚረዱ ፖሊሲዎችን ፡ ሕጎችንና ደንቦችን ያዘጋጃል ። ሲፈቀዱም ተግባራዊ የሚሆኑበትን ስልት ይቀይሳል ፡ በሥራ ላይ መዋላቸውን ይከታተላል ፡ ይቆጣ ጠራል ፡ የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ወደ ሀገር ሲገባና ወደ ውጭ አገር ሲላክ ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን የጥራት ደረጃ አጠባበቅ መመሪያ እንዲወጣ ያደርጋል ፡ የንግዱንም እንቅስቃሴ ይከታተላል ፡ ' ' ፫ " ለውጭና ለአገር ውስጥ ገበያ ለሚቀርቡ እንስሳት የማረፊያ ቦታዎችን ከነሙሉ ድርጅታቸው ጋር ያቋቁማል ፡ እንዲቋቋሙ ያበረታታል ፡ የመጓጓዣ ዘዴዎችም እንዲመቻቹ አግባብ ካላቸው መሥሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ጋር በመሆን ይከታተላል ፡ - ፬ . ወደውጭ አገር ለሚላኩና ወደ አገር ውስጥ ለሚገቡ እንስሳት ፣ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ የመቆጣጠሪያ ኳራንቲን ጣቢያዎች ያቋቁሟል ፡ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመሆን የኳራንቲን አገልግሎት እንዲሰጥ ያደርጋል ፡ ፭ ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን የእንስሳት ገበያዎችን ፡ ቄራዎችንና የቆዳና ሌጦ ማደራጃ መጋዘኖችን እንዲ ደራጁ አገልግሎታቸውም እንዲስፋፋ ያደርጋል ፡ ፮ . ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ለውጭ ገበያ ማዘጋጃና ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲቋቋሙ ዓለም አቀፍ መስፈርት እንዲጠበቅ እንዲሟላ ያደርጋል ፡ የብቃት ማረጋገጫ ይሰጣል ፡ ፡ ፯ . በእንስሳት ፡ በእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ንግድ ( ለሚሰማሩ የአገር ውስጥ ላኪና አስመጪ ነጋዴዎች . ሊያሟሏቸው ስለሚገቡ ሁኔታዎች መስፈርት ያወጣል ፡ ለሚመለከታቸው ክፍሎችም መረጃ ይሰጣል ፡ ፰ ከተለያዩ ሀገሮች ጋር የንግድ ግንኙነት በመፍጠር በውጭ አገር የእንስሳት ፥ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ገበያ የሚስፋፋበትን መንገድ ይቀይሳል ፡ ፱ አግባብ ካላቸው መሥሪያ ቤቶችና ድርጅቶች ጋር በመሆን ለእንስሳት የጉዞ አቅጣጫን ይወስናል ፡ የጉዞ ሥርዓትን መመሪያ ያወጣል ፡ የዝውውርሥርዓቱን ይከታ ፲ . የዓለም አቀፍና አገር ውስጥ የእንስሳት ምርት ተዋጽኦ ገበያ ሁኔታን እየተከታተለ ወቅታዊ የገበያ መረጃ በማሰ ባሰብ ተንትኖ ለአርቢዎች ፡ ለአገር ውስጥና ውጪ ተጠቃ ሚዎችና ነጋዴዎች ያሰራጫል ፡ " ፲፩ . የእንስሳት ፡ የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ገበያ ምርምርና ጥናት እንዲካሄድ ያበረታታል ፡ የምርምርና ጥናት ውጤቶችን ለተጠቃሚዎቹ ያሰራጫል ፡ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ግብይቱን ለማፋጠን የሚረዳ ተግባራዊ ጥናት ያካሂዳል ፡ ፲፪ ፡ ባለሥልጣኑ ለሚሰጠው አገልግሎት ክፍያ ለመሰብሰብ መመሪያ በማውጣት ያስወስናል ፡ ሲፈቀድም በተግባር ያውላል ፡ ፲፫ : ከሚመለከታቸው ጋር በመተባበር የእንስሳት የእንስሳት ምርትና ተዋጽኦ ልማት የሚዳብርበት ሁኔታ እንዲ መቻች ያበረታታል ፡ ደጋ ገጽ Lደ፳፬ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፵፭ ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፲ ዓ . ም . ፲፬• የቆዳና ሌጦ ምርት ከእርድ ጀምሮ ገበያ እስኪደርስ ድረስ - ጥራቱ የሚጠበቅበትን መንገድ ይከታተላል ፡ ፡ ፲፭ - ከክልሎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር የቴክኒክ እገዛና | ምክር ይሰጣል ፡ ! , : : . . . . : : : . . . . ! ! - ፲፮ ዓላማውን ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱና የማይንቀሳቀሱ - - 1 ንብረቶች ባለቤት ይሆናል ፡ ውል ይዋዋላል ; በስሙ ይከሳል ፡ ይከሰሳል ። ፮ . የባለሥልጣኑ አቋም { ን : : : ) : 1 : 1 | ባለሥልጣኑ : : ን ! ! ! : . . ፩ - የሥራ አመራር ቦርድ ( ከዚህ በኋላ “ ቦርዱ ” እየተባለ 6 የሚጠራ ) ፡ ፪ . በቦርዱ አቅራቢነት በመንግሥት የሚሾም አንድ ሥራ - አስኪያጅ : እና : : : : . . : ሌሎች ሠራተኞች . . . . . . . . . ፰ የቦርዱ አባላት ' ቦርዱ በመንግሥት የሚሰየሙ ሰባት አባላት ይኖሩታል ። ፱ . የቦርዱ ስብሰባ ፩ ቦርዱ በየ፫ ወር አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል ፡ | ሆኖም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በማናቸውም ጊዜ አስቸኳይ • ስብሰባ ሊያደርግ ይችላል ። ፪ ከቦርዱ አባላት ከግማሽ በላይ የሆኑት ከተገኙ ምልዓተ ጉባዔ ይሆናል ። ፫ ፣ የቦርዱ ውሳኔዎች በድምጽ ብልጫ ያልፋሉ ፡ ሆኖም ድምጽ እኩል በእኩል የተከፈለ እንደሆነ ሰብሳቢው ወሳኝ ድምጽ ይኖረዋል ። 17 1 : : : : : 6 የዚህ አንቀጽ ድንጋጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ፡ ቦርዱ . . የራሱን የስብሰባ ሥነ ሥርዓት ደንብ ሊያወጣ ይችላል ። | 10 . Powers and Duties of the Board - ፲ የቦርዱ ሥልጣንና ተግባር • ቦርዱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፡ ፩ . ባለሥልጣኑ ' በዓላማው መሠረት ተግባራዊ እንቅስቃሴ | ማድረጉን ያረጋግጣል ፡ የባለሥልጣኑን ሥራዎች በበላ - 1 . 2 ይነት ይመራል ፡ ይቆጣጠራል ፡ የአጭርና የረጅም ጊዜ - ዕቅድና ዓመታዊ የሥራ ፕሮግራምና በጀት ለመንግሥት እያቀረበ ያስወስናል ፡ ፪ በባለሥልጣኑሥራ አስኪያጅ በሚቀርቡ ሌሎች የፖሊሲ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ፡ ይወስናል ፣ . . . ፫ ለባለሥልጣኑ ሥራ አስኪያጅ አጠቃላይ የሥራ መመሪያ ' ' ይሰጣል ፡ : 1 : ! ' . . . ፩ በሥራ አስኪያጁ የሚቀርብለትን የሥራ ፕሮግራምና ' ' የበጀት ጥያቄ ይመረምራል ፡ ሲፈቀድም ተግባራዊነቱን ፲፩ የሥራ አስኪያጁ ሥልጣንና ተግባር _ ፩ : ሥራ አስኪያጁ ተጠሪነቱ ለቦርዱ ሆኖ የባለሥልጣኑ ዋና . ሥራ አስፈጻሚ በመሆን የባለሥልጣኑን ሥራዎች ይመራል ። . . . . . . . . . . . ፪ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) አጠቃላይ አነጋገር | እንደተጠበቀ ሆኖ ፡ ሥራ አስኪያጁ ፡ : : ያ ፡ ሀ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፯ የተመለከተውን የባለሥል | : : : : 1 ጣኑን ሥልጣንና ተግባር ሥራ ላይ ያውላል ፡ ለ ) በፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ሕግ መሠረት የባለሥል | ጣኑን ሠራተኞች ይቀጥራል ፡ ያስተዳድራል ፡ ገጽ ፯፻፷፭ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፴፭ ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፲ ዓ•ም• ሐ ) የባለሥልጣኑን የሥራ ፕሮግራምና በጀት ያዘጋጃል ፡ ሲፈቀድም በሥራ ላይ ያውላል ። መ ) ለበለሥልጣኑ በተደፈቀደለት በጀትና የሥራ ፕሮግራም መሠረት ገንዘብ ወጪ ያደርጋል ፡ ሠ ) ባለሥልጣኑ ከሦስተኛ ወገኖች ጋር በሚያደርጋቸው ግንኙነቶች ሁሉ ባለሥልጣኑን ይወክላል ፣ ረ ) ስለ ባለሥልጣኑ የሥራ እንቅስቃሴና ሂሳብ ሪፖርት ያቀርባል ። ፫ ሥራ አስኪያጁ ለባለሥልጣኑ የሥራ ቅልጥፍና በሚያስ ፈልግ መጠን ከሥልጣንና ተግባሩ በከፊል ለባለሥልጣኑ የሥራ ክፍልኃላፊዎች በውክልና ሊያስተላልፍይችላል ። ፲፪ . በጀት ባለሥልጣኑ ከሚሰበስበው የአገልግሎት ክፍያ ፡ ከማናቸውም ሌላ ምንጭ ከሚያገኘው ገቢ እና ከመንግሥት በሚመደብለት የበጀት ድጎማ ይተዳደራል ። ፲፫ የሂሣብ መዛግብት ፩ . ባለሥልጣኑ የተሟሉና ትክክለኛ የሆኑ የሂሣብ መዛግብት ይይዛል ። ፪ የባለሥልጣኑ የሂሣብ መዛግብትና ገንዘብ ነክ ሰነዶች በዋናው ኦዲተር ወይም እርሱ በሚሰይማቸው ኦዲተሮች | 14 . Power to Issue Regulations በየዓመቱ ይመረመራሉ ። ፲፬ ደንብ የማውጣት ሥልጣን የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህን አዋጅ ለማስፈጸም ደንብ ሊያወጣ ይችላል ። ፲፭ የተሻሩና ተፈጻሚነት የሌላቸው ሕጐች ፩ . የሚከተሉት ሕጎች በዚህ አዋጅ ተሽረዋል ፡ ሀ የከብት እርባታና የሥጋ ቦርድ አዋጅ ቁጥር ፪፻፲፪ ለ የከብት እርባታና የሥጋ ቦርድን ለማቋቋም የወጣ ትዕዛዝ ቁጥር ፴፬ / ፲፱፻፶፮ ። ፪ . ማንኛውም ሌላ ሕግ ወይም የተለመደ አሠራር ከዚህ | 16 . Effective Date አዋጅ ጋር ወይም በዚህ አዋጅ መሠረት ከሚወጡደንቦች ጋር የሚቃረን ሆኖ ከተገኘ ይህን አዋጅ በተመለከቱት ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚነት አይኖረውም ። ፲፮ አዋጁ የሚጸናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፲ ዓም ጀምሮ የጸና ይሆናል ። አዲስ አበባ ሰኔ ፴ ቀን ፲፱፻፲ ዓ . ም ዶ / ር ነጋሶ ጊዳዳ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት