×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
አዋጅ ቁጥር ፫፻፴፩/፲፱፻፶፭ ኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ክልከላ ኮንቬንሽን ማስፈፀሚያ አዋጅ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ዘጠነኛ ዓመት ቁጥር ፲፩ አዲስ አበባ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፱፻፲፭ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ አዋጅ ቁጥር ፪፻፴፩ ፲፱፻፶፭ ዓም ኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ክልከላ ኮንቬንሽን ማስፈፀሚያ ገጽ ፪ሺ፩፻፷፪ አዋጅ ቁጥር ፫፻፴፩ ፲፱፻፲፭ የኬሚካል የጦር መሣሪያዎችን ዝግጅት ፣ መመረት ፣ ክምችትና በጥቅም ላይ መዋል ለመከልከልና እነዚህንም ለማውደም የተደረገውን ኮንቬንሽን ለማስፈጸም የወጣ አዋጅ የኬሚካል ጦር መሣሪያዎችን ዝግጅት ፣ መመረት ፣ ክምችትና በጥቅም ላይ መዋል ለመከልከልና እነዚህንም ለማውደም እ.ኤ.አ ጃንዋሪ ፲፫ ቀን ፲፱፻፫ በፓሪስ የተደረገውን ኮንቬንሽን ከፈረሙት አገሮች ኢትዮጵያ አንዷ በመሆኗ ፣ ይህንኑ ኮንቬንሽን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የካቲት ፲፬ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው ስለሆነና ፣ ለዚህም አዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻፴፰ የወጣ በመሆኑ ፣ በኮንቬንሽኑ መሠረት እያንዳንዱ አባል አገር የገባውን ግዴታ ለመወጣት የሚያስችለውን እርምጃ መውሰድ እንዳለበት የተደነገገ | adopt the necessary measures to implement its obligation በመሆኑና ለዚህም አገር አቀፍ የሆነ ሕግ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፣ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ - መንግ ሥት አንቀጽ ፵፯ ( ፩ ) እና ( ፲፪ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ፩ . አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ክልከላ ኮንቬንሽን ማስፈፀሚያ አዋጅ ቁጥር ፫፻፴፩ ፲፱፻፲፭ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖ.ሣ.ቁ : ዝሸኽ ገጽ ፪ሺ፩፻፷፫ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፩ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ፪ : ት ር ጓ ሜ የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ አዋጅ ውስጥ ፣ “ ኮንቬንሽን ” ማለት የኬሚካል ጦር መሣሪያዎችን ዝግጅት ፣ መመረት ፣ ክምችትና በጥቅም ላይ መዋል ለመከልከልናእነዚህንም ለማውደም እኤአ ጃንዋሪ ፲፫ ቀን ፲፱፻፶፫ በፓሪስ የተደረገው ኮንቬንሽን ነው ። ፪ “ የኬሚካል ጦር መሣሪያ ” ማለት የሚከተሉትን ሁሉንም በአንድነት ወይም በተናጠል ማለት ነው ፣ ሀ ) በኮንቬንሽኑ ላልተከለከሉ ዓላማዎች ከሚውሉት ፣ ዓይነታቸውና መጠናቸው ከዚሁ ዓላማ ጋር የሚስማማ ከሆኑት በስተቀር መርዛማ ኬሚካሎችና ፕሪከርሰሮቻቸው ፣ ለ ) በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ ፪ ( ሀ ) የተገለጹትን መርዛማ ኬሚካሎች በመጠቀም ሞትና ሌላ ዓይነት ጉዳት ለማስከተል እንዲችሉ ሆነው የተሠሩ ጥይቶችና ለዚሁ ተግባር ብቻ የሚውሉ ሌሎች መጠቀሚያዎች ፣ ሐ ) በዚህ አንቀጽ በንዑስ አንቀጽ ፪ ( ለ ) የተጠቀሱትን ጥይቶችና መጠቀሚያዎች በቀጥታ በጥቅም ላይ ለማዋል እንዲያስችል ሆኖ የተሠራ መሣሪያ ። ፫ . “ ሚኒስቴር ” ወይም “ ሚኒስትር ” ማለት እንደቅደም ተከተሉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ወይም ሚኒስትር ነው ። ፬ . “ ሰው ” ማለት ማንኛውም በሕግ የሰውነት መብት የተሰጠው ወይም የተፈጥሮ ሰው ነው ። ፭ “ መርዛማ ኬሚካል ” ማለት ከማንኛውም ምንጭ የተገኘ ወይም በማንኛውም ዓይነት ዘዴና በማምረቻ ተቋማት ወይም በጥይቶች ውስጥ ወይም በሌላ ቦታ የተመረተ በኬሚካላዊ ውጤቱ በሕይወት ሂደት ላይ ሞትን ፣ ጊዜያዊ የችሎታ ማጣትን ወይም ቋሚ ጉዳትን በሰውና በእንስሳት ላይ ሊያደርስ የሚችል ማንኛውም ኬሚካል ፮ . “ ፕሪከርሰር ” ማለት በማንኛውም ዘዴ የመርዛማ ኬሚካል ማምረት ሂደት ውስጥ በጥቅም ላይ የሚውል ተፀግባሪ ኬሚካል ሲሆን ማንኛውንም ወሳኝ የክልኤ ወይም የብዙ ምንዝር ኬሚካላዊ ዘዴን ያጠቃልላል ፤ ፯ . “ በኮንቬንሽኑ ያልተከለከሉ ዓላማዎች ” ማለት የሚከ ተሉት ዓላማዎች ማለት ነው ፣ ሀ ) ለኢንዱስትሪያዊ ፣ ለእርሻ ፣ ለምርምር ፣ ለሕክምና ፣ ለመድሃኒት ወይም ለሌሎች ሰላማዊ ዓላማዎች መገልገያነት፡ ለ ) ለመከላከል ዓላማዎች ማለትም መርዛማ ኬሚካ ሎችና የኬሚካል ጦር መሣሪያዎች የሚያስከት ሉትን ጎጂነት ከመከላከል ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ዓላማዎች ፣ ሐ ) የኬሚካል የጦር መሣሪያዎችን ከመጠቀም ጋር ያልተያያዙና የኬሚካሎችን ለጦርነት ተግባር በመጠቀም ላይ ያልተመሰረቱ ወታደራዊ ዓላማዎች መ ) የአገር ውስጥ አድማ የመቆጣጠር ተግባርን ጨምሮ ሕግ የማስፈጸም ዓላማዎች ። ፰ “ ሠንጠረዥ ” ማለት ከዚህ አዋጅ ጋር የተያያዘው የመርዛማ ኬሚካሎችንና ፕሪከርሰሮቻቸውን ዝርዝር የያዘው የኮንቬንሽኑ ሠንጠረዥ ፩ ፣ ፪ እና ፫ ነው ፣. ፱ . “ የአድማ መበተኛ ኬሚካል ” ማለት ማንኛውም በሠን ጠረዡ ውስጥ ያልተጠቀሰ ኬሚካል ሆኖ ለኬሚካሉ መጋለጥ እስኪቋረጥ ድረስ በሰዎች ላይ በአጭር ጊዜ የሚቋረጥ የስሜት ህዋሳት መቆጣትን ወይም የአካላዊ ብቃት ማጣትን የሚፈጥር ማንኛውም ኬሚካል ነው ፣ ፬ገጽ ፪ሺ፩፻፷፬ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፩ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፱፻፲፭ ዓም ፲ . “ ድርጅት ” ማለት በኮንቬንሽኑ አንቀጽ ፰ መሠረት የተቋቋመው የኬሚካል የጦር መሣሪያዎች አስወጋጅ ድርጅት ነው ፣ ፲፩ “ ኢንስፔክሽን ” ማለት በኮንቬንሽኑ መሠረት ድርጅቱ ወይም በዚህ አዋጅ መሠረት ሚኒስቴሩ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያደርጉት ከኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ፣ ከመርዛማ ኬሚካሎችና ፕሪከርሰሮቻቸው እና በሠን ጠረዡ ካልተዘረዘሩ እራሳቸውን የቻሉ ኦርጋኒክ ኬሚካሎች ጋር የተያያዘ ምርመራ ነው ፣ ፲፪ • “ የኢንስፔክሽን ቡድን ” ማለት በድርጅቱ ተወክለው በኢትዮጵያ ውስጥ ምርመራ የሚያካሂዱ ኢንስፔክተሮች እና ረዳቶቻቸው ናቸው ፣ ፲፫ . “ እራሱን የቻለ ኦርጋኒክ ኬሚካል ” ማለት በኬሚካላዊ ስም ፣ በመዋቅራዊ ቀመር ( የሚታወቅ ከሆነ ) እና በኬሚካል አብስትራክት አገልግሎት ምዝገባ ቁጥር ( ካለ ) ሊለይ የሚችል ከኦክሳይዶቹ ፣ ከሰልፋይዶቹና ከሜታል ካርቦኔቶቹ በስተቀር ሁሉንም የካርቦን ውህዶች ከያዙት የኬሚካል ውህደት የሚመደብ ማንኛውም ኬሚካል ፲፬ • “ ተቀብሮ የተተወ ኬሚካል ጦር መሣሪያ ” ማለት እ.ኤ.አ. ከጃንዋሪ ፩ ቀን ፲፱፻፳፭ በኋላ በአንድ አገር የግዛት ክልል ውስጥ ኬሚካሉ የተቀበረበት አገር ስምምነት ሳይኖር ተቀብሮ የተተወ የኬሚካል ጦር መሣሪያ እና አሮጌ የኬሚካል ጦር መሣሪያ ጭምር ማለት ፫የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሥልጣንና ተግባር ሚኒስቴሩ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባር ይኖሩታል ፣ ፩ በኮንቬንሽኑ ኢትዮጵያ ያገኘቻቸውን መብቶች እና የገባቻ ቸውን ግዴታዎች ሁሉ መንግሥትን ወክሎ ይፈጽማል ፣ ፪ የኮንቬንሽኑንና የዚህን አዋጅ አፈጻጸም በተመለከተ የተዘጋጁ ፖሊሲዎችን ለመንግሥት ውሳኔ ያቀርባል ፤ ፫ . የኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ስምምነት አፈፃፀምና የአማካሪ ቦርድን የሥራ እንቅስቃሴ ይመራል ፣ ፬ የኬሚካል ጦር መሣሪያዎችን ፣ የመርዛማ ኬሚካሎችንና ፕሪከርሰሮቻቸውን እንዲሁም ተዛማጅ መረጃዎችን ይሰበ ስባል ፣ ያጠናቅራል ፣ በኮንቬንሽኑ ኣንቀጽ ፫ መሠረት መግለጫ አዘጋጅቶ ለድርጅቱ ያቀርባል ፣ ፭ መርዛማ ኬሚካሎችና ፕሪከርሰሮች በኮንቬንሽኑ ላልተከ ለከሉ ዓላማዎች ወደ ኢትዮጵያ ለማስገባት ፣ ወደ ውጭ ለመላክ ፣ ለማምረት ፣ ለመጠቀም ፤ ለመያዝና ለማስተላለፍ ፈቃድ ይሰጣል ፣ መጠናቸውንም በኮንቬንሽኑ መሠረት ይወስናል ፣ ዝርዝሩም በመመሪያ ይወሰናል ፣ ፮ : ለሚሰጠው አገልግሎት ዋጋ ያስከፍላል ፣ • ለድርጅቱ መግለጫ ለመስጠት የሚሰበሰቡ መረጃዎችን ትክክለኛነት ያረጋግጣል ፣ የኬሚካል ኢንዱስትሪዎችን ወይንም ተቋማት አሠራር የኮንቬንሽኑን ድንጋጌዎች የማ ይቃረን መሆኑን ለማረጋገጥ በማንኛውም የኬሚካል ኢን ዱስትሪ ወይንም ተቋም ምርመራ ያደርጋል ፣ ፰ . የኬሚካል ጦር መሣሪያዎች የሚወገዱብትንና የሚወድ ሙበትን ጉዳት ከደረሰም ስለሚወሰድበት እርምጃዎች መመሪያ ይሰጣል ፣ አፈጻጸሙንም ይከታተላል፡ ፱ ለዚህ አዋጅና ለኮንቬንሽኑ አፈጻጸም የሚረዳ መዝገብ ያደራጃል ፣ ይይዛል ፣ ፲ የኮንቬንሽኑን አስፈላጊነትና ጠቀሜታ በሕዝብ ዘንድ ያስተዋውቃል ፣ ፲፩ በማንኛውም ጊዜ በቅድሚያ ማስጠንቀቂያም ሆነ ያለቅድመ ማስጠንቀቂያ በየትኛውም ቦታ ከኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ፣ መርዛማ ኬሚካሎች ፣ ፕሪከርሰሮች እና የአድማ መበተኛ ኬሚካል ጋር በተያያዘ ምርመራ ያደርጋል ፣ ፲፪- የሚስጥራዊ መረጃዎች አያያዝ በኮንቬንሽኑ ድንጋጌዎች መሠረት መሆኑን ያረጋግጣል ፣ ገጽ ፪ሺ ፩፻፷፭ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፩ ሚያዝያ ፳ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ፲፫ በኢትዮጵያ የግዛት ክልል ውስጥ በድርጅቱ የሚደረገው ኢንስፔክሽን በኮንቬንሽኑ መሠረት መሆኑን ያረጋ ግጣል ፣ ለኢንስፔክሽን ሥራው ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ፣ በኮንቬንሽኑ መሠረት ለኢንስፔክሽን ቡድኑም የአገር ውስጥ አጋዥና አስተባባሪ ሆኖ ይሠራል ፣ ፲፬ • ለኢንስፔክሽን ተግባር ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ የኢንስፔ ክሽን ቡድን አባላት በኮንቬንሽኑ ቬሪፊኬሽን አኔክስ ፪ቢ መሠረት ስለሚኖራቸው የመመርመር ሥልጣን ፣ ልዩ መብት ፣ ጥበቃ እና ስለሌሎች ጠቃሚ መረጃዎች መታወቂያ ይሰጣል ፣ ፲፭ ከሚመለከታቸው መሥሪያ ቤቶች ጋር በመተባበር ከኬሚካል ጦር መሣሪያዎችና መርዛማ ኬሚካሎች የመከ ላከል ብሔራዊ ፕሮግራም ያወጣል ፣ ተግባራዊነቱንም ይከታተላል ፣ ከድርጅቱና ከስምምነቱ ኣባል አገራት ጋር ለሚደረገው የሥራ ግንኙነት ብሔራዊ ተጠሪ አካል ሆኖ ይሠራል ፣ ፲፮ ከዚህ አዋጅ አፈጻጸም ጋር የተያያዙ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትን ያከናውናል ። ፬ የጉምሩክ ባለሥልጣን ኃላፊነት ፩ . የጉምሩክ ባለሥልጣን ከዚህ አዋጅ ጋር በተያያዘው | 4. Responsibility of the Customs Authority ሠንጠረዥ የተጠቀሱት መርዛማ ኬሚካሎች እና ፕሪከር ሰሮቻቸው ከኢትዮጵያ ሲወጡና ሲገቡ በሚኒስቴሩ ፈቃድ የተሰጠባቸውና መጠናቸውም በፈቃዱ መሠረት መሆኑን የማረጋገጥ ግዴታ አለበት ፣ ፪ • የጉምሩክ ባለሥልጣን ይዞታቸው ከዚህ አዋጅ ጋር በተገናኘ አጠራጣሪነት ያላቸው ገቢና ወጭ ዕቃዎችን ከኣገር እንዲወጡ ወይም ወደ አገር እንዲገቡ ከመፈቀዱ በፊት ሚኒስቴሩን ማማከር አለበት ። ፭ የኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ስምምነት አፈፃፀም አማካሪ ተጠሪነቱ ለሚኒስቴሩ የሆነ የኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ስምምነት አፈፃፀም ኣማካሪ ቦርድ ( ከዚህ በኋላ “ ቦርድ ” እየተባለ የሚጠራ ) በዚህ አዋጅ መሠረት ተቋቁሟል ፣ ቦርዱ በሚኒስትሩ አቅራቢነት በመንግሥት የሚመደቡ ሰባት አባላ ይኖሩታል ፣ ሚኒስ ወይም እርሱ የሚወ ክለው የሚኒስቴሩ ባልደረባ የቦርዱ ሰብሳቢ ይሆናል ። ፮ የቦርዱ ሥልጣንና ተግባር ቦርዱ የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፣ ፩ የኮንቬንሽኑንና የዚህን አዋጅ አፈጻጸም በተመለከተ ሚኒስ ቴሩን ያማክራል ፣ ፪ • ከኮንቬንሽኑና ከዚህ አዋጅ አፈጻጸም ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ፖሊሲዎችን እያመነጨ ለሚኒስቴሩ ውሳኔ ያቀርባል ፣ ፤ የቦርዱ ስብሰባ ፩ ቦርዱ ቢያንስ በስድስት ወር አንድ ጊዜ መደበኛ ስብሰባ ያደርጋል ፣ ሆኖም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በማናቸውም ጊዜ አስቸኳይ ስብሰባ ሊያደርግ ይችላል ፣ ፪ . በቦርዱ ስብሰባ ላይ አብዛኞቹ አባላት ከተገኙ ምልዐተ ጉባዔ ይሆናል ፣ ፫ ውሣኔ የሚተላለፈው በአብላጫ ድምጽ ሲደገፍ ይሆናል ፣ ሆኖም ድምፁ እኩል የተከፈለ እንደሆነ ሰብሳቢው ወሳኝ ድምዕ ይኖረዋል ፣ ፬ . የዚህ አንቀጽ ድንጋጌ እንደተጠበቀ ሆኖ ቦርዱ የራሱን የስብሰባ ሥነ - ሥርዓት ደንብ ሊያወጣ ይችላል ። ፰ የኬሚካል የጦር መሣሪያዎችን ስለ መከልከል ማንኛውም ሰው በማናቸውም ሁኔታ የሚከተሉትን ተግባራት መፈጸም አይችልም ፣ ፩ . የኬሚካል ጦር መሣሪያዎችን ማዘጋጀት፡ ማምረት፡ መያዝ ፣ ማከማቸት ፣ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ለማንኛውም ሌላ ሰው ማስተላለፍ እና የኬሚካል ጦር መሣሪያዎችን መጠቀም ፣ ፪ • በኮንቬንሽኑ እና በዚህ አዋጅ መሠረት የተከለከሉ ተግባራት እንዲፈጸሙ በማንኛውም ሁኔታ ማንኛውንም ሌላ ሰው መርዳት ፣ ማበረታታት ወይም መገፋፋት ፣ የኬሚካል ጦር መሣሪያዎችን ለመጠቀም ወታደራዊ ዝግጅት ማድረግ ፣ ፲፪ ድርጅቱ ስለሚያደርገው ኢንስፔክሽን ገጽ ፱ሺ፩፻፷፮ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፩ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓም : ፫ የአድማ መበተኛ ኬሚካልን እንደጦር መጠቀም ። ፱ ክልከላ ስለማይኖርባቸው ሁኔታዎች ፩ በኮንቬንሽኑ ላልተከለከሉ ዓላማዎች ለመጠቀም ፈቃድ የተሰጠው ማንኛውም ሰው በሠንጠረዡ የተዘረዘሩትን መርዛማ ኬሚካሎችናፕሪከርሰሮቻቸውን ወደ ኢትዮጵያ ማስገባት ፣ ወደ ውጭ መላክ ፣ ማምረት ፣ ማደባለቅ ማዋሃድ መጠቀም ፣ መያዝና ማስተላለፍ ይችላል ፣ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፰ የተጠቀሰው ክልከላ በኮንቬን ሽኑና በዚህ አዋጅ መሠረት የኬሚካል ጦር መሠረያ ዎችን ኣገልግሎት በማይሰጡበት ሁኔታ ከማስወገድ ፣ የኬሚካል ጦር መሣሪያ ጥቃትን እና በጥቃቱ የሚደር ሰውን አደጋ ከመከላከል ጋር በተያያዘ በሚኒስቴሩ በሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ ተፈጻሚነት የለውም ። ፲ ስለመረጃ እና መዛግብት ስለመያዝ ፩ . ማንኛውም በዚህ አዋጅ መሠረት ፈቃድ የተሰጠው ወይም በሠንጠረዥ ያልተዘረዘሩ እራሳቸውን የቻሉ ኦርጋኒክ ኬሚካሎችን የሚያመርት ወይም የአድማ መበተኛኬሚካሎች ያሉት ሰው መዝገብ የመያዝ ግዴታ አለበት ፣ ፪ . ማንኛውም ሰው ከኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ፣ ከመርዛማ ኬሚካሎችና ፕሪከርሰሮቻቸው እና በሠንጠረዥ ካልተዘ ረዘሩ እራሳቸውን የቻሉ ኦርጋኒክ ኬሚካሎች ጋር በተያያዘ መረጃ ወይም ሰነድ እንዲያቀርብ በሚኒስቴሩ ሲጠየቅ የማቅረብ ግዴታ አለበት፡ ፫ . ማንኛውም ሰው ከዚህ አዋጅ ወይም ከኮንቬንሽኑ አፈፃፀም ጋር በተገናኘ ያገኘውን መረጃ በሚስጢር የመጠበቅ ግዴታ አለበት ፣ ሆኖም መረጃዎቹ ሊሰጡ የሚችሉት ፣ ሀ ) የመረጃው ባለቤት በሆነው ሰው ፈቃድ ፣ ወይም ለ ) ኢትዮጵያ በኮንቬንሽኑ የገባችውን ግዴታ እንድ ትወጣ ለማድረግ ፣ ወይም ሐ ) ይህን አዋጅ ለማስፈፀም ፣ ወይም የሕዝብን ደኅንነት ለመጠበቅ ሲባል ለሚከናወኑ ተግባራት ብቻ ነው ። ፲፩ . የመተባበር ግዴታ ማንኛውም ሰው ይህን አዋጅ ለማስፈጸም ከሚነስቴሩ ጋር የመተባበር ግዴታ አለበት ። ፩ : የድርጅቱ የኢንስፔክሽን ቡድን በኮንቬንሽኑ መሠረት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ ከኬሚካል ጦር መሣሪያዎች ፣ ከመርዛማ ኬሚካሎችና ፕሪከርሰሮቻቸው እንዲሁም በሠንጠረዡ ካልተዘረዘሩ እራሳቸውን የቻሉ ኦርጋኒክ ኪሚካሎች ጋር የተያያዘ ኢንስፔክሽን ሊያደርግ ይችላል ፣ ፪ የኢንስፔክሽን ቡድኑ አባላት በማንኛውም ቦታ ሲጠየቁ መታወቂያቸውን ት ግዴታ አለባቸው ። ፲፫ . ቅ ጣ ት በወንጀለኛ መቅጫ ሕግ የበለጠ ቅጣት የሚያስቀጣ ካልሆነ በስተቀር ፣ ፩ በማንኛውም ሰው በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ እና ፲፩ የሠፈሩትን ድንጋጌዎች ተላልፎ ሲገኝ ከአንድ እስከ ሦስት ዓመት በሚደርስ እሥራት እና ከብር ፭ሺህ ( አምስት ሺህ ብር ) እስከ ፲ሺህ ( አሥር ሺህ ብር ) በሚደርስ ገንዘብ ይቀጣል ፣ ፪ • ማንኛውም ሰው ከሚኒስቴሩ ፈቃድ ሳይኖረው በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) የተጠቀሱትን ተግባራት ሲፈፅም ቢገኝ ከሦስት እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እሥራት እና ከብር ፲ሺህ ( አሥር ሺህ ብር ) እስከ ፴ሺህ ( ሠላሳ ሺህ ብር ) በሚደርስ ገንዘብ ይቀጣል ፣ ፫ . ማንኛውም ሰው ከዚህ አዋጅና ከኮንቬንሽኑ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ ሀሰተኛ መረጃ ያቀረበ ወይም በድርጅቱ ወይም በሚኒስቴሩ የሚደረገውን ምርመራ ያደናቀፈ እንደሆነ ከአምስት ዓመት እስከ አሥር ዓመት በሚደርስ እሥራት እና ከብር ፴ሺህ ( ሠላሳ ሺህ ብር ) እስከ ፱ሺህ ( ሃምሳ ሺህ ብር ) በሚደርስ ገንዘብ ይቀጣል፡ ሚኒስቴሩ ይህን አዋጅ ለማስፈፀም ስልጉ የሕዝብ / 17. Issuance of Directives ገጸ ፪ሺ፩፻፲፯ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፲፩ ሚያዚያ ፳፩ ቀን ፲፱፻፶፭ ዓ.ም ፬ • ማንኛውም ሰው ፣ ሀ ) የኬሚካል የጦር መሣሪያዎችን የሠራ ፣ ያመረተ ፣ ያከማቸ ፣ በማንኛውም ሁኔታ ለሌላ ሰው ያስተላለፈ ፣ ወደ አገር ውስጥ ያስገባ ወደ ውጭ የላከ ፣ የገዛ ፣ ለሽያጭ ያቀረበ ፣ በአደራ ያስቀመጠ ፣ የያዘ ፣ ያመላለሰ ወይም ያደለ እንደሆነ ከአሥር እስከ ኣሥራ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ። ወንጀሉን የፈጸመው በአፍቅሮተ ነዋይ ሲሆን በተጨማሪ እስከ አምስት ሺ ብር በሚደርስ መቀጮ ይቀጣል ፣ ሆኖም ወንጀሉ የተፈጸመው የሕግ ሰውነት አዋጅ ለማስፈጸም በተሰጠው አካል የሆነ እንደሆነ የገንዘቡ ቅጣት እስከ ሦስት እጥፍ ሊደርስ ይችላል ፣ ለ ) የአመጽ መቆጣጠሪያ ኤጀንቶችን እንደጦር መሣሪያ የተጠቀመ ሰው ከአምስት እስከ አሥር ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ፣ የኬሚካል የጦር መሣሪያዎችን የተጠቀመ ወይም የኬሚካል የጦር መሣሪያዎችን ለወታደራዊ ዓላማ ለመጠቀም ዝግጅት ያደረገ እንደሆነ ከአሥር እስከ ሃያ አምስት ዓመት በሚደርስ ጽኑ እሥራት ይቀጣል ። ሆኖም የወንጀሉ አፈጸጸም ከባድ የሆነ እንደሆነ በሞት ይቀጣል ። ፲፱ : ስለመውረስ ሚኒስቴሩ በዚህ አዋጅ መሠረት ፈቃድ ሳይሰጥባቸው የገቡ ወይም የሚወጡ በሠንጠረዡ የተመለከቱትን መርዛማ ኬሚካሎችና ፕሪከርሰሮች ለመውረስ ይችላል ፣ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እንደተጠበቀ ሆኖ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፪ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) እና ( ፬ ) ላይ የተመለከ ቱትን በመተላለፍ ጥፋተኛ ሆኖ በተፈረደበት ሰው ላይ ፍርድ ቤቱ ከዋናው ቅጣት ጋር በማጣመር በሠንጠረዡ የታቀፉ ኬሚካሎች እና የኬሚካል ጦር መሣሪያዎች እንዲወረሱ ለማዘዝ ይችላል ። ፲፭ ተፈፃሚነት የማይኖራቸው ሕጎች ይህን አዋጅ የሚቃረን ማንኛውም ሕግ ወይም የአሠራር ልማድ በዚህ አዋጅ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት አይኖረውም ። ፲፮ ደንብ ስለማውጣት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ይህን አዋጅ ለማስፈጸም የሚያስ ፈልጉ ደንቦችን ሊያወጣ ይችላል ። ፲፯ መመሪያ ስለማውጣት ** « ፲፰ አዋጁ የሚፀናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፱፻፲፭ ዓ.ም ጀምሮ የፀና ይሆናል ። አዲስ አበባ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፲፱፻፲፭ ዓም ግርማ ወልደጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?