×
ያስሱ ምርቶች ስለ እኛ ይግቡ / ይመዝገቡ አግኙን English
African Law Archive
Logo
አዋጅ ቁጥር 256/1994 የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ ኣካላትን አደረጃጀት ለማሻሻል የወጣ አዋጅ

      ይቅርታ፣ ማተም አይፈቀድም።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ስምንተኛ ዓመት ቁጥር ፪ አዲስ አበባ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፲፬ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጠባቂነት የወጣ ኣዋጅ ቁጥር ፪፻፶፮ / ፲፱፻፶፬ ዓም የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን አደረጃጀት ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ... ገጽ ፩ሺ፮፻፳፱ አዋጅ ቁጥር ፪፻፶፮ / ፲፱፻፲፬ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን አደረጃጀት ለማሻሻል የወጣ አዋጅ የቀድሞው ኣስፈፃሚ አካል አደረጃጀት ለሥራ ጥራትና ቅልጥፍና አመቺ የነበረ ባለመሆኑ ፣ መርሀ ግብሩን በተገቢው የሥራ ቅልጥፍና መፈፀም ያለበት | ecutive body was not conducive for the brilliance and በመሆኑ ፣ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን አደረጃጀት ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ፣ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት አንቀጽ ፶፭ ( ፩ ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል ። ክፍል አንድ ፩ . አጭር ርዕስ ይህ አዋጅ “ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን አደረጃጀት ለማሻሻል የወጣ አዋጅ ቁጥር | 1. Shor Title ፪፻፶፮ / ፲፱፻፲፬ ” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል ። ፪ . ትርጓሜ በዚህ አዋጅ ውስጥ ፣ ፩ . “ አዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፷፯ ” ማለት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻፯ ነው ፣ ፪ ክልል ” ማለት በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ ፵፯ የተመለ ከተው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አባል የሆነ ክልል ነው ፣ ፫ “ ሚኒስቴር ” ማለት በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ ( ፩ ) የተመለከ ተውን ጽሕፈት ቤት ይጨምራል ። ያንዱ ዋጋ ነጋሪት ጋዜጣ ፖ.ሣቁ : ፰ሺ፩ ገጽ ፩ሺ፮፻፴ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፪ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓም ክፍል ሁለት ስለሚኒስትሮች ፫ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አባልነት ፩ . የሚኒስትሮች ምክር ቤት የሚከተሉት አባላት ይኖሩታል ሀ ) ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ለ ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ሐ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፬ የተመለከቱትን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የሚመሩ ሚኒስትሮች ፣ መ ) ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአባልነት እንዲሳተፉ የሚመ ርጣቸው ሌሎች ባለሥልጣኖች ፣ ፪ . በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ( ሐ ) የተመለከተው ማንኛውም ሚኒስትር በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ሊገኝ በማይችልበት ጊዜ ምክትሉ ወይም ከአንድ በላይ ምክትሎች ካሉ በግልጽ ተለይቶ ውክልና የተሰጠው ምክትል ፣ በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ በምትክ አባልነት ይሳተፋል ። ፫ . በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) የተመለከተው ምክትል እንደአግባቡ በሚኒስትር ፣ በሚኒስትር ዴኤታ ወይም በምክትል ሚኒስትር ደረጃ ሊሆን ይችላል ። ፬ የሚኒስቴሮች መቋቋም የሚከተሉት ሚኒስትሮች በዚህ አዋጅ ተቋቁመዋል ፣ ፩ . የአቅም ግንባታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ፣ ፪ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ፣ ፫ የገጠር ልማት ሚኒስቴር ፣ የመሠረተ ልማት ሚኒስቴር ፣ ፭ የገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ፣ • የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ፣ ፯ የግብርና ሚኒስቴር ፣ ፰ የትምህርት ሚኒስቴር ፣ ፱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፣ ፲ የፍትሕ ሚኒስቴር ፲፩ የገቢዎች ሚኒስቴር ፣ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ ፲፬ . የማስታወቂያ ሚኒስቴር ፣ የውሃ ሀብት ሚኒስቴር ፣ ፲፮ የወጣቶች ፣ የእስፖርትና የባህል ሚኒስቴር ፣ የማዕድን ሚኒስቴር ፲፰ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ። ፭ ተጠሪነት ፩ የሚከተሉት አስፈጻሚ አካላት ተጠሪነት ለአቅም ግንባታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ይሆናል፡ ሀ ) የትምህርት ሚኒስቴር ፣ ለ ) የኢትዮጵያ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኮሚሽን ፣ ሐ ) የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ፣ መ ) የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ፣ ሠ ) የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ ረ ) የፍትሕና የሕግ ሥርዓት ምርምር ኢንስቲትዩት ። ረ ) የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎኔ . … . ) ገጽ ፩ሺ፮፻፴፩ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፪ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ • ም • ፪ የሚከተሉት አስፈጻሚ አካላት ተጠሪነት ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ይሆናል ፣ ሀ ) የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባለሥልጣን ፣ ለ ) የኢትዮጵያ የጥራትና የደረጃዎች ባለሥልጣን ፣ ሐ ) የቡናና ሻይ ባለሥልጣን ፣ መ ) የመንግሥትየልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ባለሥ ሠ ) የመሠረታዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኢንዱ ስትሪ ኤጀንሲ ፣ ረ ) የኢትዮጵያ የውጭ ንግድ ማስፋፊያ ኤጀንሲ ፣ ሰ ) የኢትዮጵያ ፕራይቬታይዜሽን ኤጀንሲ ፣ ሽ ) የእንስሳት ገበያ ባለሥልጣን ። ፫ የሚከተሉት አስፈጻሚ አካላት ተጠሪነት ለገጠር ልማት ሚኒስቴር ይሆናል ፣ ሀ ) የግብርና ሚኒስቴር ፣ ለ ) የአደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኮሚሽን ፣ ሐ ) የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተሃድሶና ልማት ፈንድ ፣ መ ) ብሔራዊ የዕፅዋት ዘር ኢንዱስትሪ ኤጀንሲ ፣ ሠ ) ብሔራዊ የማዳበሪያ ኢንዱስትሪ ኤጀንሲ ፣ ረ ) የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ድርጅት ፣ ሰ ) የሕይወታዊ ሀብት ጥበቃና ምርምር ኢንስቲ ሸ ) የኢትዮጵያ የገጠር ኢነርጂ ልማትና ማስፋፊያ ማዕከል ። ፬ የሚከተሉት አስፈጻሚ አካላትና የልማት ድርጅቶች ተጠሪነት ለመሠረተ ልማት ሚኒስቴር ይሆናል ፣ ሀ ) የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ፣ ለ ) የአየር ትራንስፖርት ባለሥልጣን ፣ ሐ ) የመንገድ ትራንስፖርት ባለሥልጣን ፣ መ ) የመንገድ ፈንድ ጽሕፈት ቤት ፣ ሠ ) ብሔራዊ የመጠባበቂያ ነዳጅ ዴፖዎች አስተ ሰ ) የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኤጀንሲ ፣ ሸ ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኤጀንሲ ፣ ቀ ) የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ፣ በ ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ፣ ተ ) የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ። ፭ የሚከተሉት አስፈጻሚ አካላት ተጠሪነት ለገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ይሆናል ፣ ሀ ) የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለሥልጣን ፣ ለ ) የኢትዮጵያ ካርታ ሥራ ባለሥልጣን ፣ ሐ ) ብሔራዊ የሥነ ሕዝብ ጉዳይ ጽሕፈት ቤት ፣ መ ) የመንግሥት ቤቶች ሽያጭ አስፈጻሚ ጽሕፈት ፮ የሚከተሉት አስፈጻሚ አካላት ተጠሪነት ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ይሆናል ፣ ሀ ) የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ፣ ለ ) የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ፣ ሐ ) ብሔራዊ የከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት ፣ መ ) የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ፣ ሠ ) የድሬዳዋ ከተማ ኣስተዳደር ። ፯ የመድኃኒት አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሥልጣን ተጠሪነት ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ይሆናል ። ፰ የሚከተሉት ኣስፈጻሚ አካላት ተጠሪነት ለገቢዎች ጽ ፩ሺ፮፻፴፪ ፌዴራል ነጋሪተ ጋዜጣ ቁጥር ፪ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ • ም • ሀ ) የፌዴራል አገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን ፤ ለ ) የጉምሩክ ባለሥልጣን ፤ ሐ ) የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ። ፀ • የሚከተሉት አስፈጻሚ ኣካላት ተጠሪነት ለማስታወቂያ ሚኒስቴር ይሆናል ፤ ሀ ) የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኤጀንሲ ፤ ለ ) የመገናኛ ብዙኃን ማሠልጠኛ ኢንስቲትዩት ። ፲ የሚከተሉት አስፈጻሚ ኣካላት ተጠሪነት ለወጣቶች ፤ የእስፖርትና የባህል ሚኒስቴር ይሆናል ፤ ሀ ) የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ፤ ለ ) የብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት ድርጅት ፤ ሐ ) የኢትዮጵያ የስብሰባ ማዕከል ፤ መ ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቲያትር ። ፲፩ የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ተጠሪነት ለማዕድን ሚኒስቴር ይሆናል ። ክፍል ሦስት የሚኒስቴሮች ሥልጣንና ተግባር ፮ . የአቅም ግንባታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የአቅም ግንባታ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት የሚከተሉት | 6 Office for the Coordination of Capacity Building ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ ፩ የሀገሪቱን የአቅም ግንባታ ፖሊሲዎች ያመነጫል ፤ ፕሮግራምና በጀት ያዘጋጃል ፤ ሲፈቀድም በሥራ ላይ ያውላል ፤ ፪ • ለሀገሪቱ አቅም ግንባታ አስፈላጊ የሆኑ የአቅም መገንቢያ አቅሞች እንዲገነቡ ያደርጋል ፤ ፫ . በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ( ፩ ) የተመለከቱትን አስፈጻሚ ኣካላት በበላይነት ይመራል ፤ ያስተባብራል ፤ ፬ የአቅም ግንባታን በማጎልበት ረገድ ለክልሎች አስፈላ ጊውን ድጋፍ ይሰጣል ፤ ፭ የአቅም ግንባታን ለማጠናከር የሚያስፈልጉ ሌሎች ተግባሮችን ያከናውናል ። ፯ . የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ፩ . የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻ T ፯ ኣንቀጽ ፲፬ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ። ፪ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ፤ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ( ፪ ) የተመለከቱትን አስፈጻሚ አካላት በበላይነት ይመራል ፣ ያስተባብራል ። ፰ የገጠር ልማት ሚኒስቴር የገጠር ልማት ሚኒስቴር የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ ፩ : የገጠር ልማት ፖሊሲ ያመነጫል ፤ ፕሮግራምና በጀት ያዘጋጃል ፤ ሲፈቀድም በሥራ ላይ ያውላል ፤ ፪ . ለገጠር ልማት አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች የሚመነጩበ ትንና ተዘጋጅተው ሊቀርቡ የሚችሉበትን ሁኔታ ያመቻቻል ፤ ፫ የምግብ ዋስትና ፕሮግራምን ይመራል ፤ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭፪ ) የተመለከቱትን ኣስፈፃሚ ኣካላት በበላይነት ይመራል ፤ ያስተባብራል ፤ ፭ የገጠር ልማትን በማስፋፋት ረገድ ለክልሎች አስፈላ ጊውን ድጋፍ ይሰጣል ፤ ፮ የገጠር ልማትን ለማስፋፋትየሚረዱ ሌሎችተግባሮችን ያከናውናል ። - ፬- የመሠረት ልማት ሚኒስቴር ፩ በአዋጅቁጥር ፬ / ፲፱፻፷፯አንቀጽ ፲፰እና በሌሎች ሕጎች ለትራንስፖርትና መገናኛሚኒስቴር ተሰጥተው የነበሩት | 9 ሥልጣንና ተግባሮች ፣ በአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፷፯ አንቀጽ ፲፭ እና በሌሎች ሕጎች ኢነርጂን በሚመለከት ለማዕ ድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር ተሰጥተው የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮችእንዲሁም በአዋጅቁጥር ፬ / ፲፱፻፷፯ በአንቀጽ ፲፮ በንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እና ( ፲፪ ) እና በሌሎች ሕጎች ለሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ተሰጥተው የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮች በዚህ አዋጅ ለመሠረተ ልማት ሚኒስቴር ተሰጥተዋል ። ገጽ ፩ሺ፮፻፴፫ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፪ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓ.ም. ፪ ) የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ፤ የመሠረተ ልማት ሚኒስቴር ፤ ሀ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ( ፬ ) የተመለከቱትን አስፈጻሚ አካላትና የልማት ድርጅቶች በበላይነት ይመራል፡ ያስተባብራል ፤ ለ ) የኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅትን የሥራ እንቅስቃሴዎች በሁለቱ አገሮች መካከል በተደረገው ስምምነት መሠረት ይከታተላል ። ፲ . የገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ፩ በአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፫፯ አንቀጽ ፲፫ እና ፲፱ እንዲሁም በሌሎች ሕጎች ለኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ሚኒስቴርና ለገንዘብ ሚኒስቴር ተሰጥተው የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮች በዚህ አዋጅ ለገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ተሰጥተዋል ። ፪ የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ፤ የገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ( ፩ ) የተመለከቱትን አስፈጻሚ ኣካላት በበላ ይነት ይመራል ፣ ያስተባብራል ። ፲፩ . የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ ሀ ) ከክልሎችጋር በመተባበር የሕዝቡ ሰላምና ፀጥታ መጠበቁን ያረጋግጣል ፤ ለ ) የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ ፵፰ እና ፳፪ ( ፮ ) ድንጋ ጌዎች እንደተጠበቁ ሆነው ፤ በክልሎች መካከል አለመግባባቶች የሚፈቱባቸውን ሁኔታዎች ያመቻቻል ፤ ሐ ) ለክልሎች በተለይም በልማት ወደኋላ ለቀሩት ክልሎች ልዩ ትኩረት በመስጠት ድጋፍ ያደርጋል ፤ መ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ( ፮ ) የተመለከቱትን አስፈጻሚ አካላት በበላይነት ይመራል ፤ ያስተባ ፪ . የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ፤ በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻ዥ፯ አንቀጽ ፲፮ በንዑስ አንቀጽ ( ፯ ) ( ፲፩ ) ለሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ተሰጥተው የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮች በዚህ አዋጅ ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተሰጥተዋል ። ፲፪ የግብርና ሚኒስቴር የግብርና ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻፫፯ አንቀጽ ፲፪ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ። • የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻፳፯ አንቀጽ ፳፩ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣን ፣ ተግባሮች ይኖሩታል ። ፲፬ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻፷፯ አንቀጽ ፳፪ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ። ፲፭ የፍትህ ሚኒስቴር የፍትሕ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻ዥ፯ አንቀጽ ፳፫ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ። ገጽ ፩ሺ፮፻፴፬ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፪ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓም : ፲፮ የገቢዎች ሚኒስቴር ለፌዴራል መንግሥት የገቢዎች ቦርድ በአዋጅ ቁጥር ፭ ፲፱፻ዥ፯ እና በሌሎች ሕጎች ተሰጥተው የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮች በዚህ አዋጅ ለገቢዎች ሚኒስቴር ተሰጥተዋል ። ፲፯ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻ T ፯ አንቀጽ ፳፮ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻፫፯ አንቀጽ ፳፭ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ። ፲፱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ፩ . ለማስታወቂያና ባህል ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፫፯ አንቀጽ ፳፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) ፣ ( ፮ ) እና ( ፱ ) እንዲሁም ማስታወቂያን በሚመለከት በሌሎች ሕጎች ተሰጥተውት የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮች ፣ በዚህ አዋጅ ለማስታወቂያ ሚኒስቴር ተሰጥተዋል ። ፪ . የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ፣ የማስታወቂያ ሚኒስቴር በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ( ፱ ) የተመለከቱትን አስፈጻሚ አካላት በበላይነት ይመራል፡ ያስተባብራል ። የውሃ ሀብት ሚኒስቴር የውሃ ሀብት ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ ፲፱፻ዥ፯ አንቀጽ ፲፯ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች | 20. Ministry of Water Resources ይኖሩታል ። ፳፩ የወጣቶች ፤ የእስፖርትና የባሕል ሚኒስቴር ፩ የወጣቶች ፣ የእስፖርትና የባህል ሚኒስቴር የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ፤ ሀ ) ወጣቱን የሚመለከቱ ፖሊሲዎችና ሕጎች ያመነጫል፡ ሲፈቀዱም ተግባራዊነታቸውን ይከ ታተላል ፤ ለ ) ጤናማና ኃላፊነት የሚሰማው ወጣት ትውልድ ለማፍራት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ይፈጥራል ፤ ሐ ) ወጣቱ የሕገ መንግሥቱን መርሆዎች መሠረት በማድረግ በዲሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ግንባታ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖረው ኣስፈላጊውን ድጋፍ ይሰጣል ። መ ) ወጣቱ የሀገሪቱን ሕዝቦች ባህል እንዲጠብቅና እንዲያዳብር ያበረታታል ፤ ሠ ) ከሚመለከታቸው አካላት በተለይም ከክልሎች ጋር በመተባበር የወጣቱን ሁለንተናዊ ሰብእና ለማዳበር የሚረዱ ሌሎች ተግባሮችን ያከና ረ ) በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፭ ( ፲ ) የተመለከቱትን አስፈጻሚ ኣካላት በበላይነት ይመራል ፥ ያስተባ ፪ • የዚህ ኣንቀጽ ንዑስ አንቀጽ ( ፩ ) እንደተጠበቀ ሆኖ ፤ በአዋጅ ቁጥር ፲፪ / ፲፱፻ዥ፯ እና በሌሎች ሕጎች ለእስ ፖርት ኮሚሽን ተሰጥተው የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮች እና በአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፫፯ አንቀጽ ፳፬ ንዑስ አንቀጽ ( ፪ ) ፡ ( ' ( ፬ ) ( ፭ ) ' ( ፯እና ( ፰ ) እንዲሁም ባህልን በሚመለከት በሌሎች ሕጎች ለባህልና ማስታ ወቂያ ሚኒስቴር ተሰጥተው የነበሩት ሥልጣንና ተግባሮች በዚህ አዋጅ ለወጣቶች ፣ የእስፖርትና የባህል ሚኒስቴር ተሰጥተዋል ። ፳፪ • የማዕድን ሚኒስቴር ማዕድንን በሚመለከት በአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፷፯ አንቀጽ ፲፭ እና በሌሎች ሕጎች ለማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር ተሰጥተው የነበሩ ሥልጣንና ተግባሮች በዚህ አዋጅ ለማዕድን ሚኒስቴር ተሰጥተዋል ። ፳፫ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፫፯ አንቀጽ ፳ እና በሌሎች ሕጎች የተሰጡት ሥልጣንና ተግባሮች ይኖሩታል ። ገጽ ፩ሺ፮፻፴፭ ፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ቁጥር ፪ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፶፬ ዓም ክፍል አራት ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች ፳፬ ስለሌሎች አስፈጻሚ ኣካላት በዚህ አዋጅ ያልተመለከተ የማናቸውም የፌዴራሉ መንግሥት አስፈጻሚ አካል ተጠሪነትም ሆነ ሥልጣንና ተግባር በተቋቋመበት ሕግ በተደነገገው መሠረት ይቀጥላል ። ፳፭ የተሻሩ ሕጎች ፩ የአዋጅ ቁጥር ፬ / ፲፱፻፫፯ አንቀጽ ፮ እና ፱ በዚህ አዋጅ ተሽረዋል ። ፪ ይህን አዋጅ የሚቃረን ማናቸውም ሕግ፡ መመሪያ ወይም የአሠራር ልምድ በዚህ አዋጅ በተመለከቱ | 26. Transfer of Rights and Obligations ጉዳዮች ላይ ተፈጻሚነት አይኖረውም ። ፳፮ መብትና ግዴታዎች ስለማስተላለፍ ፩ የትራንስፖርትና መገናኛ ሚኒስቴር እንዲሁም የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር መብትና ግዴታዎች በዚህ አዋጅ ለመሠረተ ልማት ሚኒስቴር ተላልፈዋል ። ፪ . የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ሚኒስቴር እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስቴር መብትና ግዴታዎች በዚህ አዋጅ ለገንዘብና የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ተላልፈዋል ። ፫ • የፌዴራል መንግሥት ገቢዎች ቦርድ መብትና ግዴታዎች በዚህ አዋጅ ለገቢዎች ሚኒስቴር ተላል ፬ . የማስታወቂያና የባህል ሚኒስቴር መብትና ግዴታዎች በዚህ አዋጅ ለማስታወቂያ ሚኒስቴር ተላልፈዋል ። ፭ የእስፖርት ኮሚሽን መብትና ግዴታዎች በዚህ አዋጅ ለወጣቶች ' የእስፖርትና የባህል ሚኒስቴር ተላልፈዋል ። ፮ : የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር መብትና ግዴታዎች በዚህ አዋጅ ለማዕድን ሚኒስቴር ተላልፈዋል ። ፳፯ አዋጁ የሚጸናበት ጊዜ ይህ አዋጅ ከጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፲፬ ዓም ጀምሮ የፀና አዲስ አበባ ጥቅምት ፪ ቀን ፲፱፻፲፬ ዓም ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ታተመ

ሙሉውን ሰነድ ለማየት መግባት አለብዎ

ለመግባት የኢሜል አድራሻዎን እና የይለፍ ቃልዎን ያስገቡ።
እባክህን ትክክለኛ ኢሜል አስገባ
እባክህ የኢሜል አድራሻህን አስገባ
እባክህ የይለፍ ቃልህን አስገባ
የይለፍ ቃል ቢያንስ 8 ቁምፊዎች መሆን አለበት።
የሚስጥራዊውን ቁጥር ረሳህው?