አርባ ስምንተኛ ዓመት ቍጥር ፫
የአንዱ ዋጋ 0,60
ማ ው ጫ
አዋጅ ቍጥር ፳፫ ፲፱፻፹፩
ነ ጋ ሪ ት
የሕዝብ እንደራሴዎች ምርጫ አዋጅ
♥ ኢትዮጵያ
አዋጅ ቁጥር ፳፫ ፲፱፻፹፩
የሕዝብ እንደራሴዎች ምርጫ አዋጅ
« ኢትዮጵያ ትቅደም »
ይቱብሲክ
በኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ የመንግሥት ምክር ቢት ተጠባባቂነት የወጣ
ገጽ ፵፭
ከፍተኛ የመንግሥት ሥልጣን አካል የሆነው ብሔራዊ ሸንጐ የኢትዮጵያ ሕዝብ በተቀዳጀው ዲሞክራሲያዊ መብት በመጠቀም በቀጥተኛ ተሳትፎው በመረጣቸው የሕዝብ እን ደራሴዎች አባልነት ተቋቁሞ ተግባሩን የጀመረ በመሆኑ ፤
ዲሞክሊያዊ
በዚህ አካል መቋቋምና ሥራ መጀመር የሠርቶ አደሩ ሕዝብ ቀጥተኛ የሥልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠ ቢሆንም ፤ ይህ የሥልጣን ባለቤትነት በተሟላ መልኩ እንዲገለጽ ሌሎቹ የመንግሥት የሥልጣን አካላት በተመሳሳይ ሕዝባዊ ተሳትፎ በየደረጃው መቋቋም ያለባቸው በመሆኑ ፤
ከዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ ደረጃ የሚገኙ የመንግሥት የሥልጣን አካላት ከተቋቋሙ በኋላም የሕዝብ እንደራሴዎች ምርጫ በየጊዜው በተከታታይ መከናወን ያለበት ተግባር በመሆኑ ፤
በየደረጃው ለሚገኙ የመንግሥት ሥልጣን አካላት የሕ ዝብ እንደራሴዎችን ለማስመረጥ የሚከናወነው ተግባር በወ ጥነት መካሔዱን ለማረጋገጥ በአንድ መሠረታዊ የምርጫ ሕግ እንዲመራ ማድረግ የሚያስፈልግ በመሆኑ ፤
በሕ ı መንግሥቱ አንቀጽ፷፫ | ፩ (ሀ) መሠረት የሚከተ ለው ታውጅዋል ።
አዲስ አበባ መስከረም ፲፱ ቀን ፲፱፻፹፩ ዓ.ም.
የፖስታ ሣጥን ቁጥር ፩ሺ፲፫ (1013)
በኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ሥልጣን የሠርቶ አደሩ ሕዝብ ስለመሆኑና ከዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ ደረጃ የሚገኙ የሠርቶ አደሩ ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት | the working people and that all organs of state power, from the መግለጫ የሆኑ የመንግሥት የሥልጣን አካላት በምርጫ እን ደሚቋቋሙ በሕ ı መንግሥቱ በመደንገጉ ፤